በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ የተገናኙት ሀዋሳ ከተማ እና ሰበታ ከተማ ያደረጉት የሜዳ ላይ ፍልሚያ 1 ለ 0 ሲመሩ የነበሩት ሀዋሳ ከተማዎች የኋላ ኋላ ባስቆጠሯቸው 3 ግቦች ታግዘው ሙሉ 3 ነጥብ ይዘው ወጥተዋል ።

ሁለቱም ክለቦች በስድስተኛ ሳምንት ጨዋታቸው ከተጠቀሙት ቋሙ አሰላለፍ ቅያሪዎችን አድርገው የገቡ ሲሆን በሀዋሳ ከተማ በኩል 3 እንዲሁም በሰበታ ከተማ በኩል ደግሞ 5 ያህል ለውጦችን አድርገዋል ። በሀዋሳ ከተማ በኩል ዮሀንስ ሴጌቦ ፤ ወንድማገኝ ሀይሉ እና ዳዊት ታደሰ በሰበታ ከተማ በኩል ደግሞ አንተነህ ናደው ፤ ሀይለሚካኤል አደፍርስ ፤ዘላለም ኢሳይያስ ፤ ጁኒያስ ናንጄቦ እና ዱሬሳ ሹቢሳ ጨዋታውን መጀመር የቻሉ ተጫዋቾች ናቸው ።

በጥሩ ፉክክር የተጀመረው ጨዋታ ቀስ በቀስ የኳስ ቁጥጥሩ ወደ ሰበታ ከተማዎች አድልቶ የተሻሉ ዕድሎችን ለመፍጠር ጥረቶችን አድርገው ገና በ10ኛው ደቂቃ ላይ የመጀመሪያ ግባቸውን አግኝተዋል ። ከቀኝ መስመር የተሻገረውን ዱሬሳ ሹቢሳ በግንባሩ በመግጨት ሰበታ ከተማን መሪ ያደረገ ግብ አስቆጠረ ።
ከግቡ መቆጠር በኋላ ሀዋሳ ከተማዎች መልስ ለመስጠት ሶስት ያህል ደቂቃዎች ብቻ ነበር የፈጁባቸው ። በ13ኛው ደቂቃ ላይ ከወንድማገኝ ሀይሉ የደረሰውን ኳስ በግንባሩ በመግጨት የሞከረው ኤፍሬም አሻም በግብ ጠባቂው ቢመለስበትም የተመለሰውን ኳስ በድጋሚ አግኝቶ ግብ አድርጎታል ።

ከአቻነቷ ግብ በኋላ እንደ አጀማመራቸው መሆን ያልቻሉት ሰበታ ከተማዎች በኳስ ቁጥጥሩ የተሻሉ ቢሆኑም የግብ ዕድሎችን በመፍጠሩ ረገድ በሀዋሳ ከተማ ብልጫ ተወስዶባቸው ተደጋጋሚ ሙከራዎችን ሊያስተናግዱ ችለዋል ። በዚህም 35ኛ ደቂቃ ላይ ከቀኝ መስመር ወደ የተሻገረለትን ኳስ በግንባር በመግጨት ብሩክ በየነ ሀዋሳ ከተማን መሪ ያደረገ ግብ አስቆጠረ ።

ከመምራት ወደ መመራት የተቀየሩት ሰበታ ከተማዎች ቀደም ባሉት ደቂቃዎች ተሽለው ለመንቀሳቀስ የሞከሩ ሲሆን ከግቡ መቆጠር ጥቂት ደቂቃዎች በኋላ በሳሙኤል ሳሊሶ አማካኝነት ከቅጣት ምት ያደረጉት ሙከራ በግብ ጠባቂው ተመልሷል ። የመጀመሪያው አጋማሽመሰ በሀዋሳ ከተማ 2 ለ 1 መራነት ተጠናቀቀ ።
በተመሳሳይ ጥሩ የሜዳ ላይ ፉክክር የተጀመረው የሁለተኛው አጋማሽ ከሰባት ደቂቃዎች በኋላ ሌላ ግብ አስተናገደ ። በቃሉ ገነነ ከቅጣት ምት ያሻገረውን ኳስ ተጠቅሞ መስፍን ታፈሰ 52ኛ ደቂቃ ላይ የሀዋሳ ከተማን መሪነት ከፍ ያደረገ ግብ አስቆጠረ ።

በተቆጠሩባቸው ግቦች የተደናገጠለ የመሰሉት ሰበታ ከተማዎች ከሶስተኛው ግብ መቆጠር አምስት ደቂቃዎች በኋላ አምበላቸው በረከት ሳሙኤልን በሁለተኛ የቢጫ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቶባቸዋል ። ይህም ጨዋታውይ ይበልጥ እንዲከብዳቸው ያደረገ ሲሆን በአንዳንድ አጋጣሚዎች በፈጣን ሽግግሮች ለመፍጠር የሞከሯቸው የግብ ዕድሎች ፍሬያማ ሊሆኑላቸው አልቻሉም ። ጨዋታውን በመምራት ላይ ያሉት ሀዋሳ ከተማዎች ጨዋታውን ተቆጣጥረው ከኋላ ተነስተው ያስቆጠሯቸወን ግቦች አስጠብቀው ጨዋታውን ማጠናቀቅ ችለዋል ።

በዚህም ሀዋሳ ከተማ ነጥቡን 10 በማድረስ ወደ 6ኛ ደረጃ ከፍ ሲሉ በአንፃሩ በውድድር አመቱ እስካሁን ምንም ጨዋታ ማሸነፍ ያልቻለው ሰበታ ከተማ በ4 ነጥብ ባለበት 15ኛ ደረጃ ላይ ለመቆየት ተገዷል ።
አስተያየት ይስጡ