“ክለባችን ትልቅ ክለብ ነው ጥሩ የቡድን ስብስብ መያዛችን በአመቺው የባህርዳር ስታዲየም ላይ ከጅማ የበለጠ ውጤትን ይዘን እንድንመለስ ሰፊ ድርሻን ይጫወታል ።”
“በትልቅ አሰልጣኝ ስር ለመስራት በመቻሌ እድለኝነት ይሰማኛል” ዱላ ሙላቱ /ሀዲያ ሆሳዕና/
በሀድያ ሆሳዕና ጠንካራ የሊጉ ጉዞ ላይ ከመስመር እየተነሳ ቁልፍ ሚናን በመጫወት ለቡድኑ ወሳኝ ነጥቦችን በማስገኘት ላይ ይገኛል ።
ዱላ ሙላቱ በተለይም በአዳማ ቤት ያሰለጠኑትን አሸናፊ በቀለን በመከተል ወደ ሀድያ ሆሳዕና ካቀና በኋላ ቡድኑ በሚቸገርባቸው ወቅቶች ተቀይሮ በገባባቸው የጨዋታ መርሐ ግብሮች ለቡድኑ ውጤት የበኩሉን ሲወጣ ቆይቷል ።
ዱላ ሙላቱ ከ ሀትሪክ ስፖርቱ ቅዱስ ዮፍታሔ ጋር ቆይታን ሲያደርግ የጅማ ቆይታቸውን ጨምሮ በርካታ ጉዳዮችን አንስቷል ።
ስለ ጅማ ቆይታቸው . . . . . .
“በጅማ ቆይታችን ውጤታችን ትንሽ ተቀዛቅዞ የነበረበት መንገድ አንደኛው በርካታ ተጫዋቾቻችን በምግብ መመረዝ ታመውብን ነበር ። በሌሎች የጨዋታ ሳምንታት ላይ ይህ ሂደት የነበረ ሲሆን ታመውም ወደ ሜዳ የገቡ ተጫዋቾች ነበሩ ። እንደዛም ሆነ ውጤቱ ቢቀዘቅዝም ከነበሩብን ሁኔታዎች ውጤታችን ብዙም አስከፊ አልነበረም ።
ለሁለት ቀንም ቢሆን በጅማ ቆይታችን በመጠኑም ቢሆን መጉላላቶች ደርሰውብን ነበር ። ላረፍንበት ሆቴል ባለቤት በጊዜው ክፍያ ባለመፈፀሙ ምክንያት ሁለት ቀናትን በእግር በመጓዝ ሌላ ቦታ ለመመገብ ተገደን ነበር ። ደሞዝ ይገለፅ እንደነበረው ዘግይቷል ይህም የሆነው ስራ አስፈፃሚ የሽግግር ጊዜ ላይ በመሆኑ ሲሆን እስከ አሁንም ክፍያ አልተፈፀመልንም ።”

ተቀይሮ በመግባት ስለሚያሳየው ብቃት . . . .
“ሁሌም ተቀይሬ ስገባ አንድ ነገር ይዤ መውጣት እንዳለብኝ እረዳለሁ ፣ ሁሌም ወደ ሜዳ ስገባ በንፁህ አእምሮ እና በጎ ነገር እሰራለሁ ብዬ ስለምገባ እየተሳካልኝ ነው ። ማንም ተጫዋች ተቀያሪ ወንበር ላይ መቀመጥን አይወድም ። ሆኖም ግን የሚያስቀምጡክ አስገዳጅ ሆኔታዎች ይኖራሉ ፣ ነግር ግን በተሰጡክ እድሎች ያለህን ነገር አድርገህ ጥሩ ነገር ለመስራት ሁሌም ወደ ሜዳ መገባት እንዳለበት ይሰማኛል ።”
ሀድያ ሆሳዕና ባህር ዳር ላይ . . . .
“የባህርዳር ቀጣይ ጨዋታዎች መልካም ይሆናሉ ብዬ አምናለሁ ። ቢያንስ ጅማ ላይ የያዝናቸው ውጤቶች ባህርዳር ላይ ይኖራሉ ብዬ አላስብም የተሻለ ውጤት እንደሚኖረን አስባለው ። ክለባችን ትልቅ ክለብ ነው ጥሩ የቡድን ስብስብ መያዛችን በአመቺው የባህርዳር ስታዲየም ላይ ከጅማ የበለጠ ውጤትን ይዘን እንድንመለስ ሰፊ ድርሻን ይጫወታል ።”

ዱላ ሙላቱ እና አሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ . . . . .
ከአሸናፊ በቀለ ጋር መስራት በመቻሌ ሁሌም ደስተኛ ነኝ ፣ እሱ ትልቅ አሰልጣኝ ነው ። ሁሌም ከእርሱ ጋር በምሰራባቸው አጋጣሚዎች ሁሉ ደስተኛ ነኝ ። በትልቅ አሰልጣኝ ስር ለመስራት በመቻሌ እድለኝነት ይሰማኛል ፣ ከእርሱ ብዙ ነገሮችን እየተማርኩ እገኛለው ።
ዱላ ሙላቱ በዘንድሮው የውድድር ዓመት . . . . .
በዘንድሮው የውድድር ዓመት የእኔ ትልቁ ምኞቴ የተሻለ ተጫዋች መሆን ፣ ጎሎችን ማስቆጠር ፣ የተሻለ ነገርን ሰርቶ ማጠናቀቅ ቡድኔን ማገዝ ፣ ሁሌም ወደ ሜዳ ስገባ የተሻለ ነገርን መስራት ፣ ከእኔ የሚጠበቀውን ነገር ማድረግ ቢሆኑም ከሁሉም በላይ ግን የእኔ ትልቁ ግብ ቡድኔን በደረጃ ውስጥ ማስጨረስ ነው ።
አብሮት መጫወት ስለሚፈልገው ተጫዋች . . . .
የመስመር ተጫዋች ስትሆን የመሀል ሜዳ ተጫዋችን ትመርጣለክ ፣ እኔም ከ ብሩክ ቃልቦሬ ጋር ስጫወት በጣም ደስ ይለኛል ምክንያቴ ደግሞ ከእርሱ ጋር ሁለት አመታትን መጫወት ችያለው በእነዚህ ሁሉ ጊዜ አብሬው ስጫወት ምቾት ይሰማኛል ።

አስተያየት ይስጡ