መነሻ ገጽ ሀዲያ ሆሳዕና የሀድያ ሆሳዕና ተጫዋቾች ልምምድ አቁመዋል
ሀዲያ ሆሳዕናቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የሀድያ ሆሳዕና ተጫዋቾች ልምምድ አቁመዋል

አጋራ
አጋራ

በሊጉ የመዝጊያ ጨዋታ በ30ኛዉ ሳምንት ከሲዳማ ቡና ጋር ጨዋታቸዉን እንዲያደርጉ መርሐግብር የወጣላቸዉ ሀድያ ሆሳዕናዎች ከደሞዝ እና ጥቅማጥቅሞች ጋር ተያይዞ ልምምድ ማቆማቸዉን ሰምተናል።

የሚያዚያ ፣ ግንቦት እና የሰኔ ወራት ደመወዝ አልተከፈለንም ያሉት ተጫዋቹ ከዚህ በተጨማሪም የአምስት ጨዋታ ኢንሴንቲቭ እስከአሁን ድረስ ሊከፈለን ባለመቻሉ ምክንያት በተደጋጋሚ ቅሬታችንን ለሚመለከታቸዉ የክለቡ አመራሮች ብናቀርብም ይህ ነዉ የሚባል ምላሽ ባለማግኘታችን ምክንያት ከዛሬ ሰኔ 22 ጀምሮ ልምምድ አቁመናል ሲሉ አቋማቸዉን አሳዉቀዋል።

ከዚህ ጋር ተያይዞም የፊታችን ቅዳሜ በሰላሳኛዉ ሳምንት የሊጉ መርሐግብር ግብር ከሲዳማ ቡና ጋር የሚደረገዉን ጨዋታ እንደማይጫወቱ ተጫዋጮቹ አስረግጠው ተናግረዋል።

ይሄንን ጉዳይ በተመለከተም የክለቡ አመራሮች የተጫዋቾቹ ቅሬታ መኖሩን አምነዉ ነገር ግን ክፍያዉን ለመፈፀም አዲሱ የበጀት አመት እስኪፀድቅ ድረስ መጠበቅ እንዳለባቸው ገልፀዋል።

ዉድ የሀትሪክ ድህረገፅ አንባቢያን በዚህ ጉዳይ ላይ አዳዲስ መረጃዎች የሚኖሩ ከሆነ እየተከታተልን የምናደርስ ይሆናል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...