መነሻ ገጽ አፍሪካ ኢትዮጵያ ቡና በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ካፕ የመጀመሪያ ጨዋታዉን ዛሬ ያደርጋል !!
አፍሪካኢትዮጵያ ቡናኮንፌድሬሽን ካፕዜናዎች

ኢትዮጵያ ቡና በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ካፕ የመጀመሪያ ጨዋታዉን ዛሬ ያደርጋል !!

አጋራ
አጋራ

ኢትዮጵያ ቡና በ2013 የዉድድር አመት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግን በሁለተኝነት ደረጃ ማጠናቀቁን ተከትሎ በካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ማጣሪያ ላይ ተሳታፊ መሆኑ ይታወቃል።

የቅድመ ዉድድር ዝግጅታቸውን ለወራት ያክል በቢሾፍቱ ሲከዉኑ የቆዩት ቡናማዎቹ በአዲስ አመት ዋዜማ አርብ ምሽት የመጀመሪያ ጨዋታቸዉን ለማድረግ ወደ ዩጋንዳ አምርተዋል።

አርብ ሌሊት ዩጋንዳ የደረሱት ኢትዮጵያ ቡናዎች በትላንትናው ዕለት የመጀመሪያ ልምምዳቸዉን ጨዋታዉ በሚደረግበት በሴንት ሜሪ ስታዲየም ሰርተዋል።

በዛሬዉ ዕለትም የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታቸዉን ከዩጋንዳው Ura ስፖርት ክለብ ጋር ከቀኑ 10:00 ላይ በዩጋንዳ ሴንት ሜሪ ስታዲየም የሚያደርጉ ይሆናል።

የሁለቱን ክለቦች ጨዋታ ታንዛኒያዉያን ዳኞች የሚመሩት ሲሆን ኮሚሽነሩ ደግሞ ከሩዋንዳ መሆናቸው ታዉቋል። በተጨማሪም የሁለቱ ክለቦች ጨዋታውበሀገሪቱ የቴሌቪዥን ጣቢያ SanyukaTv እንደሚተላለፍ ተጠቁሟል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...