ከሁለት አመታት በፊት በ2014 የውድድር ዘመን ላይ የኢትዮጵያ ቡናን የተቀላቀለዉ አሰልጣኝ ነፃነት ክብሬ ከክለቡ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ለተጨማሪ ለአንድ ዓመት የሚያቆየዉን የውል ስምምነት ፈፅሟል።
አሰልጣኙ በተጠናቀቀዉ የውድድር ዘመን ከሰርቢያዊዉ አሰልጣኝ ኮቫዞቪች ኒኮላ ቡድኑን ተረክቦ በፕሪሚየር ሊጉ ሶስተኛ ደረጃን ይዘዉ ማጠናቀቅ የቻለ ሲሆን በኢትዮጵያ ዋንጫም የኢትዮጵያ ቡናን ሻምፒዮን ማድረግ ችሏል።
ኢትዮጵያ ቡና በአፍሪካ ኮንፌደሬሽን ካፕ የማጣሪያ ጨዋታ ከሳምንታት በኋላ ከኬንያው ፖሊስ ጋር ጨዋታዉን እንደሚያደርግ ይታወቃል።
- ማሰታውቂያ -



