የ ካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ የመጀመሪያ ጨዋታ በነገ እለት ከ ዛንዚባር ምላንዴግ ጋር ጨዋታ የሚያደርገ የ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አሸናፊ ኢትዮጵያ መድን ከ ጫወታው በፊት ጋዜጠዊ መግለጫ በዛሬው እለት ሂልተን ሆቴል ሰተዋል ።
በ መግለጫው ላይ የቡድኑ ዋና አሰልጣኝ የሆነው ገብረመድ ሀይሌ ለሚዲያ አካላት ስለዝግጅታቸው ገለፃ አድርገዋል ።
ኢትዮጵያ መድን 45 ቀናት በ አዲስ አበባ እና አዳማ ከተማ እንዳደረጉ የገለፁት አሰልጣኙ ዝግጅታቸውን በጥቂት ተጨዋቾች ነበር መጀመር የቻሉት አሰልጣኙ አያያይዘውም ፋይናሻል ህጉን መከተል ስለነበረብን ልጆች ለማቆይ ተቸገርን ነበር ዝግጅት እያደረግን የነረው ያሉ ሲሆን ቡድን ለ መጀመሪያ ዙር ማጣሪያ 24 ተጨዋቾችን በመያዝ እየተዘጋጀ መቆየቱን ገልፀዋል አያይዘው በቀጣይ ቀናት ቡድን ለ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተፎካካሪ ለመሆን ተጨዋች እንደሚጨምሩ ገልፀዋል።
በነገው ጨዋታ የሜዳ አድባንቴጅ ለመጠቀም የቻልነውን ሁሉ እናደርጋል : ተጋጣሚያችን አጨዋወታችው አካል ብቃት ላይ ነው በተጨማሪም የቡድኑን ሶስት ጨዋታዎች መመልከት የቻልኩኝ ሲሆን ተዘጋጅተው የሚመጡት ጎላቸውን ለመጠበቅ ነው እኛ በተቃራኒው ከመጀመሪያው ደቂቃ ጀምሮ በ ሀይ ፕሬስ ለምጫወት ወደ እንገባለን ።
- ማሰታውቂያ -

አሰልጣኙ ስለ ለቀቁ ተጨዋቾች ሲገልፁ በገንዘብ ምክኒያት ተጨዋች እንዳይጠፉ ስጋታቸውን የገለፁ ሲሆን : እንደ ቡድን ኢትዮጵያ መድን የፋይናስ ችግር የለበትም ህጉን ለማክበር ነው እንጂ በተጨማሪም ሻምፒዮን ስንሆን ጥንካሬያች መሀሉ ነበር ሁሉት የመሀል ተጨዋቾች የሉም በወጣት ለመተካት ሞክረናል ።
በመጨረሻም አሰልጣኝ ገብረመድህን ቡድኔ በሂደት በጣም አሪፍ ይሆናል በማለት መግለጫውን ጨርሰዋል ።
ጨዋታው ነገ አበበ ቢቂላ የሚደረግ ሲሆን መግቢያ ነፃ እንደሆነ ቡድኑ ገልፆል ።


