ቡናማዎቹ ሁለተኛውን የአጋማሹን ዝውውር ፈፅመዋል።
በአሰልጣኝ ሳምሶን አየለ የሚመሩት ኢትዮጵያ ቡናዎች አጥቂው ቢኒያም ጌታቸውን ወደ ስብስባቸው አካተዋል። የቀድሞው የአክሱም ከተማ ፣ ሀምበሪቾ ፣ አዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተማ አጥቂ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ከተለያየ በኋላ ያለፉትን አንድ አመት በፋሲል ከነማ አሳልፏል።
ከጎንደሩ ክለብ ጋር ለመለያየት እጅግ ፈታኝ ውይይቶች ከተደረጉ በኋላ ተጫዋቹ በመጨረሻም ከክለቡ ጋር ተለያይቶ ማረፊያው ቡናማዎቹ ቤት መሆኑን ምንጮቼ አረጋግጠውልኛል።


