የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
1. በረከት ሳሙኤል (ሃዋሳ ከተማ) ማከሰኞ ጥር 13 2017 ዓ.ም. ክለቡ ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ጋር ባደረገው የ15ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 45+2 ኛ ደቂቃ ላይ ሁለተኛ ቢጫ ካርድ የሚያስጥ ጥፋት በመፈፀሙ በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ። ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
2. አላዛር ማረነ (ድሬደዋ ከተማ) ቅዳሜ ጥር 10 2017 ዓ.ም. ክለቡ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ባደረገው የ15ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 53 ኛ ደቂቃ ላይ የተጋጣሚን ቡድን ግልፅ ግብ የማግባት ዕድል በማበላሸት በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ። ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ‥ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 3 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 63 በተቁ 1 (ሐ) እና በተቁ 2 መሰረት 3 ጨዋታ እንዲታገድ ና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 3000 /ሶስት ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
3. ያሬድ ከበደ(መቐለ 70 እንደርታ) ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።
- ማሰታውቂያ -
ፋሲል ከነማ – መቀሌ 70 እንደርታ
መቐለ 70 እንደርታ – መቻል
ኢትዮጵያ ቡና – መቀሌ 70 እንደርታ
መቀሌ 70 እንደርታ – ባህርዳር ከተማ
ኢትዮ ኤሌክትሪክ – መቀሌ 70 እንደርታ
በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35 (መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 /አንድ ሺ አምስት መቶ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።
4. ድሬደዋ ከተማ ክለቡ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ባደረገው የ15 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የድሬደዋ ከተማ ቡድን ተጫዋች የሆኑት
1 ኢስማኤል አብዱል ጋኒዩ
2 ሄኖክ ሀሰን
3 ዘርዓይ ገብረስላሴ
4 አላዛር ማረነ
በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡
5. ዋልታ አንደይ /ስሁል ሽረ – ለዕለቱ ጨዋታ ያልተመዘገበ ተጫዋች ክለቡ ከአርባ ምንጭ ከተማ ጋር በነበረው የ15ኛ ሳምንት ግጥሚያ ከተቀያሪ ውጪ የሆኑ ተጫዋቾች በሚቀመጡበት ቦታ ላይ ሆኖ ዳኞችን በተደጋጋሚ አስፀያፊ ስድብ ስለመሳደቡ እና በዚህም ምክኒያት በፀጥታ ኃይሎች ስታድየሙን ለቆ እንዲወጣ ሲደረግ ያልተገባ ባህሪ ስለማሳየቱ ሪፖርት ቀርቦበታል ። ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈጸመው ጥፋት በኢ እ‥ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 3 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 66 በተቁ 1 መሠረት 3/ሶስት/ ጨዋታ እንዲታገድና ብር 3000 /ሶስት ሺህ / እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።


