በአሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ እየተመሩ በተጠናቀቀው የዉድድር አመት ከከፍተኛ ሊጉ ምድብ ሀ የአንደኝነት ደረጃን በመያዝ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ማደግ የቻሉት መከላከያዎች በዛሬዉ ዕለት የመስመር አማካዩን ቢኒያም በላይ በአንድ አመት የኮንትራት ዉል ማስፈረማቸዉ ታውቋል።
በቀጣዩ የዉድድር አመት በሊጉ ጠንካራ ተፎካካሪ ሆነዉ ለመቅረብ ይረዳቸው ዘንድ ከሳምንታት በፊት በቢሾፍቱ ዝግጅታቸውን የጀመሩት መከላከያዎች የቀድሞዉን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፣ ስከንደርቡ ፣ ስሪያንስካ ፣ ኡሚያ እና ሲዳማ ቡና ተጫዋች የነበረዉ የመስመር ተጫዋች ወደ ስብስባቸዉ መቀላቀላቸው ተረጋግጧል።