መነሻ ገጽ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ሲዳማ ቡና እና ሰበታ ከተማ ቅጣት ተላልፎባቸዋል
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዲሲፕሊን ውሳኔ

ሲዳማ ቡና እና ሰበታ ከተማ ቅጣት ተላልፎባቸዋል

አጋራ
አጋራ

ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ27ኛ ሳምንትን ተከትሎ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ተወስነዋል።

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ማከሰኞ ሰኔ 14 2014 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ የተደረጉ ፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያ(ዎች)ከዳኞች እና ከታዛቢዎች የቀረቡለትን የዲሲፕሊን ሪፖርት ከመረመረ በኋላ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎችን አሳልፏል።

በተጫዋቾች መኳንንት ካሳ(ሲዳማ ቡና) ሁለተኛ ቢጫ ካርድ የሚያሰጥ ጥፋት በመፈፀሙ ቀይ ካርድ አይቶ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ 1 ጨዋታ እንዲታገድ እንዲሁም ያሬድ ባየህ(ፋሲል ከነማ) በ5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ የተመለከተ ተመሳሳይ 1 ጨዋታ እንዲታገድና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 /አንድ ሺ አምስት መቶ/ እንዲከፍል ተወስኗል።

በክለቦች ሲዳማ ቡና የክለቡ አምስት ተጫዋች በሳምንቱ ጨዋታ በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍል ሰበታ ከተማ በ27 ኛ ሳምንት ቅድመ ጨዋታ ስብሰባ ላይ የክለቡ ቡድን መሪ ባለመገኘቱ በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የውድድር ደንብ መሰረት ክለቡ ብር 5000/አምስት ሺህ/ እንዲቀጣ ተወስኗል።

ዋና ዳኞች ቢኒያም ወርቅአገኘው ፣ ተካልኝ ለማ እና ዳንኤል ግርማይ ሰኔ 7 2014 ዓ.ም በተደረገው የ26ኛ ሳምንት ቅድመ ጨዋታ ስብሰባ ላይ ስላለመገኘታቸው ሪፖርት የቀረበባቸው በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የውድድር ደንብ መሰረት እያንዳንዳቸው ብር 1000/አንድ ሺህ/ እንዲቀጡ ውሳኔ ተላልፏል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...