የባህርዳር ከተማው ዋና አሰልጣኝ ደግአረግ ይግዛው በባህርዳር ከተማ ለተጨማሪ ሁለት አመታት የሚያቆያቸውን ውል አራዝመዋል።
ክለቡ የአሰልጣኙን ውል ማራዘም ይፋ ያደረገ ሲሆን በሌሎች ክለቦች ይፈለጉ እንደነበርም አያይዞ ገልጿል።
አሰልጣኝ ደግአረግ ባህርዳር ከተማን እየመሩ ክለቡን የኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ተሳታፊ ማድረጋቸውም ይታወሳል።
አሰልጣኙ ባህርዳር ከተማን እየመሩ በፕሪሚየር ሊጉ ባደረጓቸው 94 ጨዋታዎች በ45 አሸንፈው ፣ በ29 አቻ ሲለያዩ በ20 ተረተዋል።
- ማሰታውቂያ -



