ሳሙኤል ሳሊሶ ወልቂጤ ከተማን ተቀላቅሏል!
የፊት መስመሩ ተጫዋች ሳሙኤል ሳሊሶ ከመቐለ 70 እንደርታ ጋር በስምምነት ከተለያየ በሃላ በደግአረገ ይግዛው የሚመራውን ወልቂጤ ከተማን ተቀላቅሏል ::
ሳሙኤል ሳሊሶ የዝውውር መስኮቱ በነገው እለት ከመጠናቀቁ በፊት በክትፎዎቹ ቤት የሚያቆየውን የአንድ አመት ኮንትራት በይፋ መፈረሙ ተገልጿል ::
ሳሙኤል ሳሊሶ ከዚህ በፊት በሼር ኢትዮጵያ ፤ መከላከያ እንዲሁም መቐለ 70 እንደርታ እንደርታ በመጫወት አሳልፏል ::