መነሻ ገጽ ወልዋሎ ወልዋሎ አዲግራት ዩንቨርሲቲ የቀድሞ አሰልጣኙን ለመቅጠር ከጫፍ ደርሷል
ወልዋሎዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ወልዋሎ አዲግራት ዩንቨርሲቲ የቀድሞ አሰልጣኙን ለመቅጠር ከጫፍ ደርሷል

አጋራ
አጋራ

 

ከአሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ ጋር ከቀናቶች በፊት የተለያዩት ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ
የቀድሞ አሰልጣኛቸው ብርሀኔ ገብረእግዚአብሔርን ለመቅጠር ከጫፍ ደርሰዋል ::

የቀድሞ ኪራይ ቤቶች፣ ኢትዮጵያ መድህን፣አዳማ ከተማ እና መቐለ አሰጣኝ ብርሀነ ገብረእግዚአብሄር ወልዋሎ አዲግራት ዩንቨርሲቲን ከከፍተኛው ሊግ ወደ ፕሪምየር ሊግ ያሳደገ አሰልጣኝ ሲሆን። በ2010 የፕሪምየር ሊግ ወድድር ዘመን ወልዋሎን ጠንካራ ተፎካካሪ አድርገውት እንደነበሩ የሚታወስ ነው። በተለይም አሰልጣኙ የሚሰሯቸው ቡድኖች ኳስ ተቆጣጥሮ የሚጫወት ቡድን መሆናቸው እና የወልዋሎን አጨዋወት ባህል ጠንቅቅው የሚያውቁ ከሞሆናቸው የተነሳ አሰልጣኙን የወልዋሎ ቀዳሚ ተመራጭ እንዳደረጋቸው ተነግሯል። ፊርማቸውንም በጥቂት ቀናቶች ውስጥ አሳርፈው ምናልባትም በ 15ኛው ሳምንት ከአንድ አመታት በኋላ ወደ ሜዳው በመመለስ ወልቂጤ ከተማን የሚያስተናግደው ወልዋሎን እየመሩ ወደ ሜዳ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል። አሰልጣኙ የመውረድ ስጋት የተጋረጠበት ወልዋሎን የማዳን ሀላፊነት ተጥሎባቸዋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

ዋልያዎቹ በአሜሪካ የወዳጅነት ጨዋታን ሊያደርጉ ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ አሜሪካ ሊያመራ ነው ነገር ግን የወቅቱ የብሔራዊ ቡድኑ...