መነሻ ገጽ ሀትሪክ ስፖርትጋዜጣ በጣም የሚወዷት እና ሁሌም የሚያነቧት ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣዎ ነገ ለገበያ ትቀርባለች።
ሀትሪክ ስፖርትጋዜጣዜናዎች

በጣም የሚወዷት እና ሁሌም የሚያነቧት ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣዎ ነገ ለገበያ ትቀርባለች።

አጋራ
አጋራ

በጣም የሚወዷት እና ሁሌም የሚያነቧት ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣዎ ነገ ለገበያ ትቀርባለች።

ሀትሪክ በነገው እትሟ ምንን ታስነብቦት ይሆን?
በሀገር ውስጥ ዘገባ የስፖርቱ ባለውለተኞችን የተነጠቅንበት ጥቁር ሣምንት ነበርና
የእሸቴ ገበየሁ “ኳስ ፊደሉ” ህልፈት ብዙዎቹን ስላሳዘነበት በአትሌትክሱ መንደር ታላላቅ ድሎችን ለማስመዝገብ እየተንደረደረ የነበረውና በተለያዩ አለም አቀፍ ውድድሮች በአጭር ርቀት ሀገሩን በመወከል ባንዲራዋ ከፍ ብሎ እንዲውለበለብ ሲተጋ ስለነበረው አትሌት አባዲ ገና በለጋ እድሜው በድንገት በሞት ስለመነጠቃችን እንደዚሁም በተጫዋችነትና በመከላከያ እግር ኳስ ክለብ ውስጥ በቴክኒክ ዳይሬክተርነትና በተለያየ ኃላፊነቶች በመስራት የሚታወቀው ዋስይሁን ማሞ በተመሳሳይ በሞት የተለየን ስለመሆኑ መሪር ሀዘን ተሰምቶን ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጆቻቸው መፅናናትን በመመኘት ዘገባን ሰርተናል።
ሀትሪክ በሌላ የሀገር ውስጥ ዘገባዋ
“ጠንክረህ ስራ እንጂ ከሜዳ ውጪም ማሸነፍ ይቻላል፤ መሪነታችንን አሁንም አጠናክረን እንቀጥልበታለን” ያለውን የቅዱስ ጊዮርጊሱን
ደስታ ደሙንም አቅርቦላታለች።
ሌላው ከፍተኛ ተወዳጅነት ባተረፈላት THE BIG INTERVIEW በሚለው አምዷም የአዳማ ከተማው ዳዋ ሁቴሳ
“ከሁሉም ጨዋታ ቀላሉ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር የምናደርገው ነው……..“እኛ እየተጫወትንበት ያለው የአዳማ ማሊያ ሳይቀየር ዘንድሮ 5ኛ አመቱን ይዟል ስለማለቱና የአዳማን ማሊያን ባደረግኩበት አራት አመታት በቅዱስ ጊዮርጊስ ስላለመሸነፋቸው ይናገራል።
ሀትሪክ በባህር ማዶ ዘገባዋም የሊቨርፑል የስኬት ሚስጥር ተጨዋች ስለሆነው ፋብያኖን አስመልክቶና ብራዚላዊው ኔይማር ስለ ቡድኑ አጋር እና ተጨዋች ምባፔ ምርጥ ብቃት ስለመናገሩ እንደዚሁም ሌሎች ዘገባዎች አሏት። ያንብቧት። የፊት ለፊት ገጿም ይህንን ይመስላል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...