ለ17 አመት በታች የሴቶች የአለም ዋንጫ
ለማለፍ እየተደረገ ባለው የማጣርያ ጨዋታ ላይ እየተካፈለ የሚገኘው የብሩንዲ ከ17 አመት በታች የሴቶች ብሄራዊ ቡድን የታንዛኒያ አቻቸውን ቅዳሜ ዕለት ቡጁምቡራ ላይ ያስተናግዳሉ፡፡ ይህን ጨዋታ ኤርትራዊያን አርቢትሮች ሲመሩት ኢንተርናሽናል አርቢትር ሊዲያ ታፈሰ 4ኛ ዳኛ በመሆኗ አርብ ዕለት ወደስፍራው ታቀናለች፡፡
በተመሳሳይ የማጣሪያ ጨዋታ ላይ የሚካፈለው የኢትዮጵያ ከ17 አመት በታች የሴቶች ቡድን ካምፓላ ላይ በኡጋንዳ የደረሰውን የ2 ለ 0 ሽንፈት ለመቀልበስ የፊታችን እሁድ ባህርዳር ላይ የመልስ ጨዋታውን ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
አስተያየት ይስጡ