መነሻ ገጽ መቐለ 70 እንደርታ ቅድመ ጨዋታ ዳሰሳ | ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ መቐለ 70 እንደርታ
መቐለ 70 እንደርታቅዱስ ጊዮርጊስቅድመ ዳሰሳዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ቅድመ ጨዋታ ዳሰሳ | ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ መቐለ 70 እንደርታ

አጋራ
አጋራ

ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ መቐለ 70 እንደርታ
የጨዋታ ቀን: እሁድ ታህሳስ 26/2012
የጨዋታ ሰዓት: 9:00
የጨዋታ አርቢትር: ኢንተ. ዳኛ ባምላክ ተሰማ
ቦታ: አዲስ አበባ ስታድየም

6ተኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ዛሬ በሚካሄደው የቅዱስ ጊዮርጊስን መቐለ 70 እንደርታ ጨዋታ ፍፃሜውን ያገኛል። መቐለ 70 እንደርታዎች ከጣፋጭ የትግራይ ደርቢ ማግስት፣ቅዱስ ጊዮርጊስ ከተካታታይ የነጥብ ማጣት ጉዞ ሚያገናኘው ይህ ጨዋታ እንደሚከተለው ዳስሰነዋል።

መቐለ 70 እንደርታ ከቡድኑ አምበል ሚኪኤለ ደስታ ወጪ በጉዳት ሆነ በቅጣት ሚያጡት ተጨዋች አይኖርም።ባሳለፍነው ሳምንት ወልዋሎን ባሸነፋበት ጨዋታ በጉዳት ተቀይሮ የወጣው ዳንኤል ደምሱ ከጉዳቱ አገግሞ ለጨዋታው ዝግጁ ሆኗል።ቅዱስ ጊዮርጊሶች በበኩላቸው ግብ ጠባቂው ልአለም ብርሃኑ፣ ናትናኤል ዘለቀ፣አቡበከር ሳኒ አሁንም ከጉዳታቸው አለማገገማቸውን ተከትሎ ከነገው ጨዋታ ውጪ ሲሆኑ ሳላሀዲን በርጌቾ፣ሳላሀዲን ሰይድ እና ፓትሪክ ማታሲ ወደ ልምምድ ተመልሰውላቸዋል።

ቀጥተኛ እና መስመር ላይ ትኩረት ያደርገ አጨዋወትን ለመተግበር ሚሞክሩት ፈረሰኞቹ መስመር ላይ ትኩረት አድርገው እድሎችን መፍጠር ሊማክሩ እንደሚችሉ ይገመታል።በተለይ በ5 ጨዋታዎች ስድስት ግቦች ያስተናገደውን የመቐለ 70 እንደርታ ደካማ የመከላከል ቅንጅትን ሰብሮ ለመግባት ከመሀልብ እና ከመስመር የሚጣሉ ኳሶች ላይ ትኩረት ያደርግሉ ተብሎ ይጠበቃል።

መቐለዎች ከወልዋሎ ጋር በነበራቸው ጨዋታ ከጉዳት ተመልሶ ጥሩ የተንቀሳቀሰውን ዮናስ ገረመውን ማግኘታቸው በአማኑኤል እና ያሬድ ከበደ ላይ ተንጠልጥሎ የነበረውን የቡድኑ እድል የመፍጠር ሀላፊነት በመጠኑም ሊቀንስ ችሏል።ከሜዳቸው ውጪ ሲጫወቱ የመልሶ ማጥቃትን አጨዋወት ተመራጭ ሚያደርጉት መቐለዎች ዛሬም በጥሩ አቋም ላይ በሚገኙት ያሬድ ከበደ ና አማኑኤል ገብረሚካኤል ላይ መሰረት ያደርገ መልሶ ማጥቃት አጨዋወትን ይዘው የመግባታቸው እድል ሰፊ ነው።በተለይ በሁለቱ ተጨዋቾች ያለው መግባባት ለቅዱስ ጊዮርጊስ ተከላካይ ክፍል ፈታኝ ሊሆን እንደሚችል ይገመታል።

መቐለ 70 እንደርታ ከሜዳው ውጪ ባደረጋቸው ሁለት ጨዋታዎች ላይ 5 ግቦችን አስቆጥሮ አራት ግቦችን ሲያስተናግድ ፈረሰኞቹ በበኩላቸው በሜዳቸው ባደረጉዋቸው ሁለት ጨዋታዎች 1 ግብ አስቆጥረው ምንም ግብ አልተቆጠረባቸውም።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...