በወቅቱ የተጨዋቾች ዝውውር ዝምታን መርጠው የቆየቱ ጅማዎች በዚህ ሳምንት የ9 ተጨዋቾች ዝውውር አጠናቀዋል።
በርካታ የመሃል ሜዳ ወሳኝ ተጨዋቾቻቸውን ያጡት ጅማ አባጅፋር ኤልያስ አህመድ ከባህርዳር ከተማ፣ሃብታሙ ንጉሴ ከወልድያ፣አብርሃም ታምራት ከደደቢት በማስፈረም የመሃል ክፍላቸውን ለማጠናከር ሞክረዋል።
ባሳለፍነው የውድድር ዓመት ከባህርዳር ከተማ ጋር ጥሩ ጊዜ ያሳለፈው ኤልያስ አህመድ የቀድሞ አሰልጣኙን ነው ፓውሎስ ጌታቸው መንገድ በመከተል ጅማ አባጅፋር ማረፍያውን ሲያደርግ፣ደደቢት ላይ በቂ የመሰለፍ አድል ያላገኘው አብርሃም ታምራት እና አምና ከፍተኛ ሊጉ ላይ ከወልድያ ከተማ ጋር ቆይታ ያረገው ሃብታሙ ንጉሴን ማስፈረም ችለዋል።
በተጨማሪ አምና በመጀመርያ ዙር ደደቢትን በ2009 ወልዋሎን በአምበልነት መምራት የቻለው ተከላካዩ ኤፍሬም ጌታቸው ሌላኛው የፓውሎስ ጌታቸው ፈራሚ ነው።
ላይ ከተጠቀሱት ተጨዋቾች በተጨማሪ ሱራፋኤል አወል ከሰበታ ከተማ፣ከአዳማ ጋር በውዝግብ የተሞላ የውድድር አመት ያሳለፈው ብዙአየው አንደሻው፣አማኑኤል ጌታቸው ከጅማ አባቡና፣ሰዒድ ይመር ከአርባምንጭ ከተማ፣ተመስገን ደረሰ ከወልቂጤ ከተማ ማስፈረም ችለዋል።
አስተያየት ይስጡ