የቅ/ጊዮርጊስ ተጨዋቾች ከጨዋታው ውጪ ሆነዋል!በኬንያ አዘጋጅነት በፈረንጆቹ በ2018 አ/ም በአገር ውስጥ ሊጎች በሚጫወቱ ተጨዋቾች ብቻ ለሚካሄደው የቻን ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ 18 ተጨዋቾችን ይዘው ጅቡቲ ተጉዘዋል ።
በመድረሱ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ውስጥ ተካተው የነበሩት የቅ/ ጊዮርጊስ ተጨዋቾች ወደ ጅቢቲ ከሚጓዛው የቻን ቡድን ውጪ ሆነዋል።
አሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ የቅዱስጊዮርጊስ ተጨዋቾችን አስመልክተው እንደሚሉት ተጨዋቾቹ ከቡድኑ ጋር አብረው ልምምድ ባለማደረጋቸው እና ከቱኒዚያ መልስ የጉዞ ድጋም በተጨዋቾቹ ስለሚኖር ከቅዳሜው ጨዋታ ውጭ ማድረጋቸውን ተናገረዋል።ከዚህ
በተጨማሪም የመከላከያው ምንይሉ ወንድሙ በጉዳት ወደ ጅቡቲ አልተጓዘም።
- ማሰታውቂያ -
ለቅዳሜ ጨዋታ የተመረጡ ተጨዋቾች
ግብ ጠባቂዎች፦
1)ጀማል ጣሰው /ጅማ አባ ቡና)
2)ለአለም ብርሃኑ /ሲዳማ ቡና/
3)ሳምሶን አሰፋ /ድሬደዋ ከተማ/
ተከላካዮች፦
4)ሙጂብ ቃሲም /አዳማ ከነማ/
5)አንተነህ ተስፋዬ /ሲዳማ ቡና/
6)አብዱልከሪም መሀመድ /ኢትዮጵያ ቡና/
7)አምሳሉ ጥላሁን/ ፋሲል ከተማ/
8)ደስታ ዮሀንስ / አዋሳ ከተማ/
9)ተስፋዬ በቀለ
አማካዮች፦
10)ጋዲሳ መብራቴ /ሀዋሳ ከነማ/
11)ሽመክት ጉግሳ /ደደቢት/
12)ሙሉአለም መስፍን /ሲዳማ ቡና/
13)ታፈሰ ሰለሞን /ሀዋሳ ከተማ/
14)ቡርክ ቃልቦሬ /ድሬዳዋ ከተማ/
አጥቂዎች፦
15)ጌታነህ ከበደ (ደደቢት)
16)አብዱራህማን ሙባረክ /ፋሲል ከነማ/
17)አዲስ ግደይ /ሲዳማ ቡና/
18 )አሚ መሀመድ /ጅማ አባቡና/