By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: “ሁለቱ ጨዋታዎች በሜዳችን ቢሆኑ ኖሮ በትንሹ አራት ነጥብ ማግኘት የምንችልበት ነበር ።” “በግል በተፈጠረ ስህተት እንጂ እንደ ቡድን ተበልጠን አይደለን የተሸነፍነው ።” “ወጣት ተጫዋቾችን መልምለን “ሻዶው” ቡድን የመስራት ዕቅድ አለኝ ።” የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ገብረመድኅን ኃይሌ
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንዜናዎችዋልያዎቹ

“ሁለቱ ጨዋታዎች በሜዳችን ቢሆኑ ኖሮ በትንሹ አራት ነጥብ ማግኘት የምንችልበት ነበር ።” “በግል በተፈጠረ ስህተት እንጂ እንደ ቡድን ተበልጠን አይደለን የተሸነፍነው ።” “ወጣት ተጫዋቾችን መልምለን “ሻዶው” ቡድን የመስራት ዕቅድ አለኝ ።” የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ገብረመድኅን ኃይሌ

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 2 years ago
Share
SHARE

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ገብረመድኅን ኃይሌ ሞሮኮ ላይ የተደረጉትን ሁለት የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎችን አስመልክቶ በዛሬው ዕለት በፌዴሬሽኑ ፅህፈት ቤት ከጋዜጠኞች ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል ።

አስቀድመው በቀዳሚው ጨዋታ ስለነበረው አየር ሁኔታ የተናገሩት አሰልጣኝ ገብረመድኅን ጨዋታው እንዲቋረጥ ብንጠይቅም ፊፋ እንዲቋረጥ አይፈልግም የሚል መልስ ነው የተሰጠን ብለዋል ።

“የአየር ሁኔታው በየጊዜው ይለያያል ። ርጥበት አዘል የአየሩ ሁኔታም አንዴ ይወጣል አንዴ ይመለሳል ። ነገር ግን እኛ የነበረው ሁኔታ ቀዝቃዛ አየር እንደነበረ እናውቃለን ። እንዳያቹት አየሩ አንዴ ይወጣል አንዴ ይመለሳል ። ሁኔታውን አይተነዋል ግን ምንም መቀየር የምንችልባቸው ሁኔታዎች አልነበሩም ። ”

- ማሰታውቂያ -

“በተጨባጭ ቢታይም በተደጋጋሚ ጥያቄዎች አቅርበናል ። ነገር ግን ፊፋ እንዲቋረጥ አይፈልግም የሚል ድርቅ ያለመልስ ነው የተሰጠን ። ”

“በተለይም ሁለተኛው አርባ አምስት ደቂቃ ላይ አስቸጋሪ ነበር ። ከኛ በተቃራኒ በካታንጋ አቅጣጫ ማለት ነው የኛንም የተቃራኒ ቡድን ተጫዋቾችን ለይተን የማናይባቸው አጋጣሚዎች ነበሩ።”

የመጀመሪያው ጨዋታ ደመናማና ቀዝቃዛ ነው ያሉት ገብረመድህን ኃይሌ ሁለተኛው ጨዋታ ደግሞ ፀሐይና ሞቃታማ የአየር ሁኔታ የነበረው መሆኑን በማንሳት የአየር ሁኔታ ለውጥ በተወሰነ መልኩ በቡድኑ ላይ ተፅዕኖ ፈጥሯል ሲሉ ተናግረዋል ።

ከቡርኪናፋሶ ብሔራዊ ቡድን ጋር በነበረው ጨዋታ ላይ ካለው የደረጃ ልዩነት ጋር በተያያዘ አስቀድመው በልምምዶች ወቅት እና ቁጭ ብለው በመነጋገር በስነ ልቦና ደረጃ እንዲዘጋጁ እና ጫና እንዳይኖርባቸው ባደረጉት ጥረት የጠበቁትን ነገር ግን እንዳላዩ ተናግረዋል ።

“በመጀመሪያዎቹ 70 ደቂቃዎች ጥሩ ነበርን በመጨረሻዎቹ 20 ደቂቃዎች ግን የጠበቅነው ያህል አልነበረም ። ጎል ካስተናገድን በኋላ ማለት ነው ። ለጨዋታው በጥሩ ዝግጅት ገብተናል ። ጎል እስካስተናገድንበት ጊዜ ድረስ በጣም በጥሩ ሁኔታ በብቃት የተቆጣጠሩበት ሁኔታ ነበረ ።”

” ከተጋጣሚም በተሻለ አጥቅተናል ። በተለይም በመልሶ ማጥቃት ብዙ ኳሶች ነጥቀን ወደ ተጋጣሚ ሜዳ ገብተን ጎል ለማስቆጠር አጋጣሚዎች ሁሉ ተፈጥረው ነበረ ። አጨራረስ ላይ ግን ጥሩ አልነበረም ። ”

አሰልጣኙ አክለውም የነበረውን የስነ ልቦና ጫና በአጭር ጊዜ መቅረፍ አይቻልም ብለዋል ።

ተጋጣሚን ኳስ በመንጠቅ በፍጥነት ለማጥቃት አስበው እንደነበረም በመናገር ተጋጣሚ እስኪደራጅ የነበሩ መዘግየቶች ግን ዋጋ እንዳስከፈላቸው ተናግረዋል ።

ስለአጨዋታቸው የተናገሩት አሰልጣኙ ለመከላከል አልገባንም ሲሉ ተናግረዋል ። “እኛ ለመከላከል አልገባንም ። ያለው ደረጃችንን እናውቀዋለን ። ግን ደሞ እኛ እንደ ቡድን ተንቀሳቅሰን እናሸንፋለን የሚል ዕምነት ነበረን ። አቀራረባችንም ለማሸነፍ ነበር ።

“ግን ወደ መጨረሻ አካባቢ አንድ ጎል ብቻ አይደለም ሶስት ጎሎች አስተናግደናል ። ግን ይሄ የተፈጠረው በግል በተፈጠሩ ስህተቶች ነው ። እንጂ እንደ ቡድን ብልጫ ወስደውብን አልነበረም ።”

እንደ ግል የነበረውን ስህተት ለማስተካከል እንደማይከብድ የተናገሩት አሰልጣኙ እንደ ቡድን ቢሆን ተስፋ ሊያስቆርጥ ይችላል ብለዋል ።

በሜዳ ላይ መጫወት ያለውን ጠቀሜታ ያነሱት አሰልጣኝ ገብረመድህን ኃይሌ ምናልባት ጨዋታዎቹ እዚህ ተደርገው ቢሆን ኖሮ ቢያንስ ማግኘት ከሚጠበቅባቸው ስድስት ነጥቦች አራት ማግኘት ይችሉ እንደነበር ተናግረዋል ።

ስለ አጨዋወት ለውጣቸው በሰጡት አስተያየትም እዚሁ ተጫውትንም ሌላ ሀገር ላይ በዚህ አጨዋወት እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል ።

አክለውም የአጨዋወት ለውጡ በተጫዋቾቹ ላይ ግርታን አልፈጠረም ብለዋል ።

በተጨማሪም ስለ ፊት መስመር አጥቂ ምርጫቸው ለተነሳላቸው ጥያቄ በሀገሪቱ ያለው የዘጠር ቁጥር ሚናን በብቃት የሚወጣ ተጫዋች ዕጥረት አለመኖሩ እንዲቸገሩ እንዳረጋቸው ተናግረዋል ።

“ኢትዮጵያ ውስጥ ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ዘጠኝ ቁጥር ተጫዋቾች አሉ ለማለት በግሌ አያስደፈረኝም ። ግን ያሉትን ዘጠኝ ቁጥሮች ወደፊትም ወስደን ማየት ይጠበቅብናል ። ነገር ግን ሌላ አማራጭ መውሰድ እንደሚጠበቅብኝ አስባለሁ ። በዛ ቦታ ላይ ሌላ ሰው ማለማመድ አስፈላጊ ሆኖ ስለተገኘ ። ምክንያቱም ያላቸው ቴክኒካል አቅም ፤ የአጨራረስ አቅማቸው ፤ የታክቲክ አረዳዳቸው ብንመለከት በየክለቦቹ የሚገኙት የዘጠኘ ቁጥሮች ሁኔታ ለብሔራዊ ቡድን አስቸጋሪ ነው።”

ወደፊት ባሉን ጊዜዎች ሰፊ ነገሮትን እንሰራለን ያሉት አሰልጣኙ በታዳጊዎች ላይ ለመስራት ያሰቡትን እቅድ ተናግረዋል ። “ለውጥ ማምጣት ከተፈለገ ብዙ ነገሮችን ማየት አለብን ። የትውልድ አንድ ቦታ ላይ የመቆም ነገር ይታየኛል ስለዚህ ወጣቶችን የምናመጣበት መንገድም አንድ ነገር ነው ።”

“ስለዚህ ለፌዴሬሽኑ በቅርቡ የማስገባው ዕቅዱ ይኖራል ። ከ23 አመት በታች ያሉ ወጣት ተጫዋቾችን መልምሎ እንደ “ሻዶው” ቡድን ለማዘጋጀት ሀሳቡ አለኝ ። ”

“የሊጉ ውድድር የሚደረግበት አንድ ቦታ ስለሆነ ከፕሪሚየር ሊግ የሚመረጡ ተጫዋቾች በተለይ ከተቻለ በሳምንት አንድ ቀንም ክለቦች ፈቃደኛ ከሆኑም በሳምንት ሁለት ቀን የምናሰራበትና በተወሰነ ከአጨዋወት ዘይቤው ጋር የመተዋወቂያ መድረክ እንዲኖራቸው ለማብቃት ማለት ነው ።”

“አሁን የተወሰኑ ብቅ እያሉ ያሉ ልጆች አሉ ። እንደነ ያሬድ ፤ ወገኔ ፣ አለምብርሐን ፣ ብርሀኑ አይነት ተጫዋቾች አሉ ። ስለዚህ እነዚህን ወጣቶች ሰብስበን በድግምግሞሽ ስራ ብሔራዊ ቡድንን መተካት ይኖርብናል ። ቢያንስ ከዚህ በአንድ ጊዜ ስድስት አልያም ሰባት ተጫዋቾች ብናመጣ እንኳን በጣም ጥሩ ነገር ነው ብዬ ነው የማስበው ።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article “ትልልቆቹን ክለቦች ጨምሮ ለሁሉም ክለቦች ከ48-68 ሺህ ብር ደጉመን እንደሻማ ቀልጠን ውድድሩን መርተናል አሁን ግንበዚህ መንገድ አይቀጥልም ” አቶ ደረጄ አረጋ / የአ/አ እግርኳስ ፌዴ.ፕሬዝዳንት/
Next Article ለቅዳሜ የተጠራው የአ/አ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጠ/ጉባኤ እያወዛገበ ነው ….

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ደቡብ ሲቲ ካኘ

​የደቡብ ክልል ካስትል ዋንጫ እጣ አወጣጥ ስነስርአት በሀዋሳ ሴንትራል ሆቴል ዛሬ 10:00 ላይተከናውኗል፡፡

Mussie Girmay By Mussie Girmay 8 years ago
ሪፖርት | ስሑል ሽረ በዲድዬ ሌብሪ ብቸኛ ግብ ኢትዮጵያ ቡናን አሸነፈ
የአትሌት ምልመላና ምርጫ ላይ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ አንድም ተሳትፎ የለውም ይሄ መታወቅ አለበት” ዶክተር አሸብር ወ/ጊዮርጊስ / የኢት.ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝዳንት/ “ያለበቂ ክፍያ የሚሰሩ አሰልጣኞች አሉን ኢትዮጵያ ሀገራቸውን አስቀድመው ክብር ለኢትዮጵያ ባንዲራ በሚል እየሰሩ በመሆናቸው እናመሰግናለን” ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ / የኢት.አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት /
እንደተለመደው ሀትሪክ ስፖርት ከአዳዲስና ወቅታዊነትን ከተላበሱ ዘገባዎቻ ጋር ነገ ማለዳ ገበያ ላይ ትውላለች ፤
ቡናማዎቹ አፄዎቹን ሲረቱ ሐይቆቹ በመጥፎ ጉዟቸው ቀጥለዋል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?