የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን በቀጣይ የሚደረጉ ተከታታይ የአለም ዋንጫ አምስት የማጣሪያ ጨዋታዎች በሞሮኮ እንደሚካሄድ አስታወቀ።
የፌዴሬሽኑ ፕሬዜዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ ከሞሮኮ አቻቸው ጋር ባደረጉት ስምምነት መሠረት አምስቱም በሜዳችን የምናደርጋቸው ጨዋታዎች በሞሮኮ የሚካሄድ ሲሆን የጨዋታዎቹ የማርኬቲንግ መብትን ስፖርቴጅ ለተሰኘው ተቋም 180 ሺህ ዶላር መሸጡን ዋና ስራ አስፈጻሚው አቶ ባህሩ ጥላሁን ተናግረዋል።
ተቋሙ ከግብጽ ብሄራዊ በድን ጋር ያለውን ጨዋታ ብቻ 140 ሺህ ብር መግዛቱ ታውቋል። የሞሮኮ ሜዳዎችን በርካታ ሀገራት የሚጠቀሙበት ሲሆን ኢትዮጵያ አንዷ እንድትሆን በመፍቀዱ አቶ ባህሩ የሞሮኮ እግርኳስ ፌዴሬሽንን አመስግነዋል