በወቅታዊው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ውድድሮች ሲሰረዙ አሁን በወጣ መረጃ የ 2020 የፊፋ ከ 20 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች መራዘማቸው ይፋ ሆኗል ።
በመጪው ወርሀ መስከረም እንዲካሄድ ቀነ ቀጠሮ ተይዞለት የነበረው በኮስታሪካ እና ፓናማ አዘጋጅነት የሚካሄደው የ 20 ዓመት በታች የአለም ዋንጫ የማጣሪያ ጨዋታዎች መቼ እንደሚካሄዱ ያልተገለፀ ሲሆን ካፍ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተነጋግሮ ውሳኔ እንደሚያስተላለፍ አሳውቋል ።
የኢትዮጵያ ከ 20 ዓመት ሴት ብሔራዊ ቡድንም የብሩንዲ አቻቸውን በሰፊ ጎል ልዩነት በማሸነፍ ከዜምቧቡዌ ጋር ለመጫወት መርሐ ግብር ወጥቶላቸው የቆየ ቢሆንም ካፍ ውድድሩን ማረዘሙን ይፋ አድርጓል ።