አሰልጣኝ ያሬድ ቶሌራን ካሰናበተ በኋላ በጊዜያዊ አሰልጣኞች ሲመራ የቆየው ኢትዮጲያ መድን ድርጅት
የቀድሞውን የሃዲያ ሆሳዕና አሰልጣኝ ግርማ ታደሰን በአንድ አመት የቆይታ ጊዜ አስፈርሞታል፡፡
ከክለቡ በተገኘ መረጃ አሰልጣኙ የመጀመሪያው ውል አንድ አመት የተስማማ ሲሆን እንደ ውጤቱ ውሉ በረጅም ጊዜ ሊራዘም እንደሚችል ተስማምተዋል፡፡ አሰልጣኙ ከትላንት በስቲያ አዲስ አበባ መጥቶ ከክለቡ ጋር ተስማምቶ የተመለሠ ሲሆን ሰኞ 3 ሰአት ላይ ስራውን ይጀምራል ተብሎ ይጠበቃል፡፡