በሊጉ በርካታ ጎሎችን በማስቆጠር ቀዳሚው ክለብ የሆኑት ሲዳማ ቡናዎች የፊት መስመራቸውን ለማጠናከር በማሰብ በሙከራ ላይ የሚገኘውን ናይጄሪያዊውን የፊት መስመር አጥቂ ኢብራሂም ሙፉታኡ ለማስፈረም መቃረባቸውን እየተነገረ ይገኛል ፡፡
ኢብራሂም ሙፉታኡ ያለፉትን ሳምንታት በሲደማ ቡና ክለብ የሙከራ ጊዜ ሲያደርግ መቆየቱ ሲታወስ በቆይታ ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ ማድረጉን ለማወቅ ቸለናል ፡፡ ኢብራሂም ሙፉታኡ በሊጉ አስደናቂ የፊት መስመር ጥምረት እያሳየ ለሚገኘው የሲዳማ ቡና ተጨማሪ ግብአት እንደሚሆን ይጠበቃል ፡፡