ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ ነገ በገበያ ላይ
ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ እንኳን ለጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለች በነገው እትሟ የተለያዩ የሀገር ውስጥ እና የባህር ማዶ ዘገባዎችን ይዛሎት ከተፍ ልትል መሰናዶዋን አጠናቃለች።
ሀትሪክ በሀገር ውስጥ የስፖርት ዘገባዋ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ባተረፈላት አምዷ የሲዳማ ቡናውን ስኬታማ አጥቂ አዲስ ግደይን ይዛሎት መጥታለች።
አዲስ ምን ምን ጉዳዮችን ለጋዜጣው ተናግሮ ይሆን?
የሚከተለው ይገኝበታል።
“በልቤ ያለው ሲዳማ ቡና ብቻ ነው፤ አሁንም ሲዳማ ቡናዊ ነኝ” ያለበት ሲጠቀስ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ስላደረጉት ጨዋታም በዳኝነቱ አልተደሰትኩም ይላል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎን አስመልክቶም እኛ ከማንም አናንስም፤ ለአፍሪካ ዋንጫም እናልፋለንም ብሏል”።
ሀትሪክ በሀገር ውስጥ ሌላ ይዛሎት የቀረበችው ተጨዋች ለኢትዮጵያ ቡና ጎሎችን ማስቆጠር የጀመረውን ሀብታሙ ታደሰን ነው። ተጨዋቹ ከወልቂጤ ከተማ ክለብ ተዘዋውሮ ከመጣ በኋላ በቡና ደስተኛ መሆኑንም ይናገራል። ስለ ቡናም ይሄንን ብሏል። “ኢትዮጵያ ቡና ከእግር ኳስ በላይም ፍቅር የሆነ ቡድንም ነው” ይላል።
ሀትሪክ በባህር ማዶ ዘገባዋም የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግን አስመልክቶ ለሊጉ መሪ ሊቨርፑል የሚጫወተው ግብጻዊው መሀመድ ሳላ ፕሪምየር ሊጉን እንዳሸነፍን አድርገን ማሰብ የለብንም ሲል ራሱን አስመልክቶም “ራስ ወዳድ የምባል አይነት ተጨዋች አይደለውም” ሲልም ይናገራል።
ሌላው የማንቸስተር ዩናይትድ አምበል መሆን ትልቅ ክብር ነው ያለው ደግሞ አሪ ማጉዋዌር ነው። የአርሰናሉ አለቃም ክለባቸው ነጥብ እየጣለ በመጓዙ ተስፋ እንደቆረጡ ተናግረዋል።
ሀትሪክ እነዚህ እና ሌሎች ሊያነባቸው የሚችሉ ዘገባ አላት። ሀትሪክ አታሞልጦት።
ሀትሪክን ከጋዜጣዋ በተጨማሪ ከፍተኛ መሻሻል ባሳየውና በአጭር ጊዜ በርካታ ጎብኚዎች ባሉት በድረ-ገፅዋም hatricksport.net አዳዲስ መረጃዎችን ያገኛሉና ዛሬውኑ ይጎብኙን።
የሀትሪክ ስፖርት የነገው የፊት ለፊት ገፅ ይህንን ይመስላል።
ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ ነገ በገበያ ላይ ሀትሪክ ስፖርት ጋዜጣ እንኳን ለጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለች በነገው እትሟ የተለያዩ የሀገር ውስጥ እና የባህር ማዶ ዘገባዎችን ይዛሎት ከተፍ ልትል መሰናዶዋን አጠናቃለች።
Managing Editor at Hatricksport Website