የኢትዮጵያ ሴቶች ከ17 ዓመት ብሔራዊ ቡድን ለዓለም ዋንጫ ለመካፈል የመጀመሪያ የማጣርያ ጨዋታውን በዛሬው ዕለት ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ ከዩጋንዳ አቻቸው ጋር በሉጎጎስታር ታይምስ ስታዲየም የሚያደርጉ ይሆናል ፡፡
ብሔራዊ ቡድኑ ዩጋንዳ ከገባ በኋላ ከጋዜጠኞች ጋር ቃለ መጠይቅ አድርጓል። የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን ምክትል ዋና ፀሀፊ አቶ ሰለሞን ከጋዜጠኞች ጋር ያደረጉትን ቃለ ምልልስ ወደ እናንተ አድርሰናል።
አቶ ሰለሞን ለጋዜጠኞች ሲናገሩ “እዚህ ዩጋንዳ ለከ17 አመት በታች የሴቶች አለም ዋንጫ ማጣሪያ ነው የደረስነው፤ ለጨዋታው ዝግጁ ነን።” ብለዋል አቶ ሰለሞን አክለውም “ለዚህ ጨዋታ ቡድናችን በሆቴል ተሰባስቦ ለ11 ቀናት ልምምድ ሲሰራ ነበር፤ ለጨዋታው በአካል ብቃትም ሆነ በስነልቦና ረገድ በጥሩ ሁኔታ ተዘጋጅተናል።” ሲሉ ተናግረዋል።
ለጨዋታው 25 አባላት ያለው ልዑክ ቡድን ወደ ስፍራው ያቀና ሲሆን ጨዋታው ዛሬ ከቀኑ 10፡00 ሲል የሚጀምር ይሆናል።
ሀትሪክ ስፖርት ድረ ገጽም ለሴት ብሔራዊ ቡድናችን መልካም እድል እንዲገጥመው ትመኛለች!
አስተያየት ይስጡ