በአሰልጣኝ ደግ አረገ ይግዛው የሚመሩት ወልቂጤ ከተማዎች ባደጉበት ዓመት በሊጉ ጥሩ እንቅስቃሴን በማሳየት ማሳለፋቸው ይታወሳል ።
ከቅዱስ ጊዮርጊስ አቡበከር ሳኒን ያስፈረሙት ክትፎዎቹ በሊጉ ልምድ አላቸው ተብሎ ከሚጠሩት የአማካይ ስፍራ አንዱ የሆነውን ፍሬው ሰለሞንን ከመከላከያ ማስፈረማቸው ይፋ ሆኗል ።
ፍፌው ሰለሞን ያለፉትን ዓመታት በመከላከያ ቤት ሲያሳልፍ በሙገር ሲሚንቶ እና በሐዋሳ ከተማም በመጫወት ማሳለፉ የሚረሳ አይደለም ።
አስተያየት ይስጡ