መነሻ ገጽ ዜናዎች የፊፋ መልዕክተኞች ጣታቸውን ወደ አስመራጭ ኮሚቴው ሰብሳቢ አዙረዋል
ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

የፊፋ መልዕክተኞች ጣታቸውን ወደ አስመራጭ ኮሚቴው ሰብሳቢ አዙረዋል

አጋራ
አጋራ

የእርስበርሳችን አለመስማማትና አለመግባባት ለሀገር ቅድሚያ አለመስጠት ችግራችን በስዊዘርላንድ ዙሪክ አደባባይ የፊፋን በር ማንኳኳት መጀመሩ በርካቶቻችሁን ያስጨነቃችሁ ጉዳይ ዛሬስ መፍትሄ ያገኝ ይሆን ???

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የፕሬዚዳንት እና የስራ አስፈፃሚ ምርጫ ለአራት ጊዜ መራዘሙን ተከትሎ ጉዳዩን ለማጣራት የአለም አቀፉ እግር ኳስ አስተዳዳሪ (ፊፋ) ተወካይ አካላት ዛሬ አዲስ አበባ መግባታቸውንና እነዚህ መልዕክተኞች በጁፒተር ሆቴል ከ 5ቱ ዕጬ ፕሬዝዳንቶች ከ9 አስመራጭ እና ከ3 ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ እንዲሁም ጊዜያዊ ዋና ፀሐፊው አቶ ሰለሞን ገ/ስላሴ ጋር በጁፒተር ሆቴል ጥልቅ ውይይት እንደሚያደርጉ የተነገረ ቢሆንም የስብሰባ ቦታው ከተባለው ሆቴል ወደ ሂልተን ዙሯል፡፡

ጥቅምት 30/2010 ዓ,ም ተብሎ እስከ የካቲት 24/2010 ዓ,ም ድረስ ለስድስት ወራት ያልተካሄደው ፕሬዝዳንታዊና ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ምርጫ አሁንም አነጋጋሪነቱ ቀጥሏል፡፡ፊፋ የመጨረሻውን ቀን ለመወሰን የላካቸው መልዕክተኞች ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ ከቀኑ
9፡30 በሂልተን ሆቴል ከማናጅመንት አባላት ጋር ውይይት ያደረጉ ሲሆን ከሰዓታት በኋላ የአስመራጭ ኮሚቴና ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ አባላትን ማነጋገራቸውም ታውቋል፡፡

የፊፋ ተወካዮች አሁን በሂልተን ሆቴል አምስቱን ዕጩ ፕሬዝዳንቶች አቶ ጁነዲ ባሻን ጨምሮ እንዲሁም ዋና ፀሐፊውን አቶ ሰለሞን ገ/ስላሴን ያካተተ ሰፋ ያለ ውይይት በማድረግ ላይ ሲሆኑ መልዕክተኞቹ የአስመራጭ ኮሚቴው ሰብሳቢ ወደ ሆኑት አቶ ዘሪሁን መኮንን ላይ ጣታቸውን በመቀሰር ፡ ምሺቱን ባለድርሻ አካላትን በቡድንና በነጥብ እያነጋገሩ ወደ መፍትሄው በር እየተጓዙ ይመስላሉ፡፡

ውሳኔ ከተወሰነና ዕጩዎች ከታወቁ በኋላ ህግ በድምጽ አይሻርም ከተባለ እዚያው መቆም ነበረበት እንጂ ከተወሰነ በኋላ ለፊፋ ደብዳቤ መጻፍ አልነበረበትም በሚል መልዕክተኞቹ ተቃውመዋል።

የአስመራጭ ኮሚቴው አባላትም አቶ ዘሪሁን የላኩት ደብዳቤ ከኮሚቴው ዕውቅና ውጪ በራሳቸው ፍላጎት ብቻ ደብዳቤውን ወደ ዙሪክ መላካቸውን ለመልዕክተኞቹ
አጋልጠዋል።

የፊፋ መልዕክተኞች ከፕሬዝዳንታዊው ዕጩዎች መካከል አቶ ተካ አስፋውን ቀደም ብለው ከደቂቃዎች በፊት በግል ያነጋገሩ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ሌላኛውን እጩ ፕሬዝዳንት ዶክተር አሸብርን በማነጋገር ላይ ናቸው።

በአሁኑ ሰዓት የፊፋ መልዕክቶች ከሚመለከታቸው የፌዴሬሽኑ አካላት ጋር በሂልተን ሆቴል የሚያደርጉትን አነጋጋሪና መፍትሄ አፈላላጊ ውይይቶች ተጨማሪ መረጃዎችን ይጠብቁን፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና የሊጉን መሪነት ሲያጠናክር ኤሌክትሪክ እና አፄዎቹም አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ሲዳማ ቡና ፣ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ እና ፋሲል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...