መነሻ ገጽ ወላይታ ድቻ ፋሲል ከነማ ከወላይታ ድቻ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ እንዲተላለፍ ጥያቄ አቀረበ
ወላይታ ድቻዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግፋሲል ከተማ

ፋሲል ከነማ ከወላይታ ድቻ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ እንዲተላለፍ ጥያቄ አቀረበ

አጋራ
አጋራ

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሊግ ኮሚቴ ፋሲል ከነማ ከወላይታ ድቻ በ11ኛ ሳምንት የፊታችን ጥር 11 ቀን ከቀኑ በ ዘጠኝ ሠዓት በፋሲለደስ ስታዲየም እንዲጫወቱ ፕሮግራም ማውጣቱ ይታወሳል ይህንን ተከትሎ የፋሲል ከነማ ቡድን የዕለቱን ጨዋታ በተጠቀሰው ቀን ለማድረግ እንደሚቸገርና ጨዋታው ወደ ሌላ ቀን እንዲዛወር በቀን 03/05/11 ለፌዴሬሽኑ በተፃፈ ደብዳቤ ጥያቄ አቅርቧል።
ፋሲል ከነማ ጨዋታው እንዲዛወርለት ፌዴሬሽኑን የጠየቀበትን ምክንያት በደብዳቤው ላይ እንዳስቀመጠው ከወላይታ ድቻ ጋር ጨዋታው በሚካሄድበት ጥር 11 ቀን በጎንደር የጥምቀት በዓል የሚከበርበት ታላቅ ቀን በመሆኑ የፀጥታ አስከባሪም ሁለት ቦታ ለመመደብ አስቸጋሪ በመሆኑ እንዲሁም የጥምቀት በዓልን በተንቀሳቃሽ ቅርስነት ለመመዝገብ የዩኔስኮ ከፍተኛ ባለሙያዎችና ቱሪስቶች ዲፕሎማቶች በብዛት የሚመጡበት ቀን በመሆኑ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ጨዋታ ማካሄድ አስቸጋሪ ሰለሆነ ጨዋታው ይተላለፍልን ሲል በደብዳቤ ጠይቋል።ፌዴሬሽኑ ለፋሲል ከነማ ጥያቄ እስከ አሁን ድምፁን ባያሰማም ጥያቄው አሳማኝ በመሆኑ የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ወደ ተስተካካይ ጨዋታ ጎራ መግባቱ አይቀሬ መሆኑን ስማችን አይገለፅ ያሉ የፌዴሬሽኑ ሠዎች በተለይ ለhatricksport.com ገልፀዋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...