መነሻ ገጽ ሀትሪክ ስፖርትጋዜጣ “ፋሲል ባልረባ ውሳኔ ተሸንፎ የሚፈረካከስ ቡድን አይደለም”  አሰልጣኝ ምንተስኖት ጌጡ (ፋሲል ከተማ)
ሀትሪክ ስፖርትጋዜጣብቸኛዋ ባለቀለም የስፖርት ጋዜጣየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግፋሲል ከተማ

“ፋሲል ባልረባ ውሳኔ ተሸንፎ የሚፈረካከስ ቡድን አይደለም”  አሰልጣኝ ምንተስኖት ጌጡ (ፋሲል ከተማ)

አጋራ
አጋራ


ኢትዮጵያ ቡናና ፋሲል ከተማ 

በበርካታ ደጋፊዎቻቸው ታጅበው ያደረጉት 

ጨዋታ በኢትዮጵያ ቡና 3ለ2 አሸናፊነት 

ተጠናቋል፡፡ ሳሙኤል ሳኑሚ፣ ኤልያስ 

ማሞና አቡበከር ናስር ለቡና ኤርሚያስ 

ሃይሉና መሃመድ ናስር ለፋሲል ጎሎቹን 

አስቆጥረዋል፡፡ የ2009 ምስጉን ዳኛ 

ተብሎ የተመረጠው ኢንተርናሽናል 

አርቢትር አማኑኤል ሃ/ስላሴ የመራው 

ጨዋታ ከፍተኛ ውዝግብ ያስነሳ ሲሆን 

ፋሲሎች በዳኛው ውሳኔ በመበሳጨት 

የክስ ሪዘርቭ ማስያዛቸው ታውቋል፡፡ 

የጨዋታው መጠናቀቅ ተከትሎ የቡናው 

ምክትል አሰልጣኝ መሃመድ ኢብራሂም 

(ኪንግ) “ዳኞችን መውቀስና መተቸት 

አልፈልግም ባላቸው አቅም እየሰሩ 

እንደሆነ አውቃለሁና” ሲል የፋሲሉ 

ምንተስኖት ጌጡ በበኩሉ “ኢትዮጵያ 

ቡና አላሸነፈንም ያሸነፈን ዳኛው ነው፡

፡ 75 በመቶ የተሸነፍነው በዳኛው ነው 

የሚመለከተው አካል ርምጃ መውሰድ 

አለበት፡፡ አገርን ወክለን ነው የመጣነው 

ብዙ ሃብት ባክኗል ውጤት ለማስለወጥ 

የሚሞክር ከሆነ ባንለፋ ይሻላል” ሲሉ 

አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ ዳኝነት ከስህተት 

የፀዳ ባለመሆኑ ጎንደር ላይ ፋሲል 

ኤሌክትሪክን 1ለ0 በረታበት ጨዋታ 

የኤሌክትሪኩ አልሃሰን ካሉሺያ ተጠልፎ 

የመሃል ዳኛው ሳህሉ ይርጋ በዝምታ 

ማለፋቸውን ተከትሎ ኤሌክትሪኮች የክስ 

ሪዘርቭ ማስያዛቸውን የሚያወሱ ወገኖች 

የፋሲሎች ቁጣ ተጋኗል ባይ ናቸው፡፡ 

የአርቢትር አማኑኤል ሃ/ስላሴ ዳኝነቱን 

የሚተቹና ለሃሪሰን ቀይ ካርድ የግድ 

መስጠት ነበረበት የሚሉ ወገኖች ደግሞ 

ዳኝነቱ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ ስህተቶች 

እንዴት ሊቀንሱ ይገባል የሚል ጥናት 

ሊሰራ ይገባል ይላሉ፡፡ የጨዋታው 

መጠናቀቅ ተከትሎ ፋሲሎች ለሊቱን 

ጎንደር የገቡ ሲሆን እሁድ ጠዋት የክለቡን 

አሰልጣኝ ምንተስኖት ጌጡን ዮሴፍ 

ከፈለኝ በስልክ አናግሯቸው የሚከተለውን 

ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

ሃትሪክ፡- ከጨዋታው እንነሳና 

እንዴት አገኘኸው?

ምንተስኖት፡- ጨዋታውን በተመለከተ 

ኳሱን መሰረት ያደረገና ማጥቃት ላይ 

የተመሰረተ ሰለሆነ ማራኪ እንደነበር 

ነው የማውቀው፡፡ በቡድኔ አጨዋወትም 

ደስተኛ ነኝ፡፡ የጨዋታ ቅመም የሚባለው 

ዳኛ ነው ተገቢ ያልሆነ ውሳኔ ሲወስን 

የተበደለው ክለብ ተጨዋቾች በስነልቦና 

ደረጃ እየወረዱ ይመጣሉ፡፡ የሚገርምህ 

እኛ እንኳን ሊበደለን ብንበደል ጭምር 

አለልን ብለን አምነን የምንገባው ዳኛውን 

ነው፡፡ ያመንከው ዳኛ ውሳኔ የተዛባ 

ከሆነ ግን ቡድንህ ይወርዳል እኛ ላይ 

የደረሰውም ይሄ ነው፡፡ 

ሃትሪክ፡- የደጋፊዎቹ የመቀባበል 

ሂደት እንዴት አገኘኸው?

ምንተስኖት፡- ይሄ ነው ኳስ፡፡ 

ደጋፊው በሙሉ እንዲህ ቢቀጥል ጥሩ 

ነው፤ የነበረው መንፈስ ደስ ይላል፡፡ 

በዘርና በሃይማኖት የተለያየውን አንድ 

የሚያደርግ ቢኖር ስፖርት ነው፡፡ እግር 

ኳስ ደግሞ ይህን የማድረግ አቅም አለው፡

፡ የደጋፊዎቹ አካሄድ በሌሎች ክለቦች 

ደጋፊዎችም መተግበር አለበት ባይ ነኝ፡፡ 

ሃትሪክ፡- ወደ ዳኝነቱ እንምጣና 

ተበድለናል የሚለው ሃሳብህ አሁን አለ?

ምንተስኖት፡- አዎ የልጆቹ ነጭ ደም 

ፈሶም ቢሆን መበደላቸው ያሳዝናል፡፡ ዳኞች 

ኮሚቴው አገር ወክለን እንደመጣን ከግምት 

ከቶ የተሻለ ዳኛ ቢመድብ ደስ ይለኛል፡፡ 

ጨዋታው ቀመር ተሰርቶበት ነው ያልኩት 

ምክንያት ስላለኝ ነው፡፡ ኢንተርናሽናል 

ዳኛ ሆነህ ስትሳሳት ሆን ተብሎ ነው ወይ 

ያስብልሃል ቀለል ያሉ ስህተቶች ሰዋዊ 

ናቸው ውጤት የሚቀይር ስህተት ሲሆን 

የቡና በረኛ መስመር አልፎ በእጁ እየነካ 

ዝም የሚል ከሆነ ግን ዳኝነቱ ለአንድ ወገን 

ነው ወይም ራሱ ይዞት የመጣ ተልዕኮ አለ 

ለማለት እገደዳለሁ፡፡

ሃትሪክ፡- አማኑኤል ሃ/ስላሴ ተልዕኮ ይዞ 

ይመጣል የሚባል አይነት ዳኛ አይደለም… 

ስህተት ነው ወይስ ርግጠኛ አንተ እንዳልከው 

ተልዕኮ ይዞ መጣ ማለት ይቻላል?

ምንተስኖት፡- ስም የሚያሰጥህኮ ስራህ 

ነው፡፡ ጥሩ ከሰራህ የሚያስከብርህ ካልሰራህ 

ደግም ተልዕኮ ይዘህ መጥተሃል ያስብልሃል፡

፡ 12 ጨዋታ ስንጫወት አንድም ቀን 

ዳኞች ላይ አሳብቤ አላውቅም ችግሮችን 

ውስጣዊ አድርገን ነው የሰራነው፡፡ ትክክለኛ 

ያልሆነ ቀይ ካርድ በራምኬል ላይ መዝዞ 

እኛ ማግኘት የነበረብንን በተለይ የሃሪሰንን 

ከውጪ ኳስ በእጁ መንካት በዝምታ ማለፉ 

ግን ስሜታችንን ጎድቷል፡፡

ሃትሪክ፡- ራምኬል ሎክ ይቅርታ 

መጠየቁስ የዳኛውን ውሳኔ ተገቢነት 

አያሳይም?

ምንተስኖት፡- በፍፁም አልጠየቀም ይሄ 

የተሳሳተ መረጃ ነው ኮሚሽነሩ ሸረፋ ደሌቾ 

አንተ ከመጀመሪያው ተነስተህ ነው የመታኸው 

ሲለው… አብረን ስንሮጥ በእንቅስቃሴ ክንዴ 

ላይ ተጋጨ ብሎ ራምኬል ሲመልስ ነው 

የሰማሁት፡፡ ይሄ ለማዘናጋት ካልሆነ በቀር 

ይቅርታ አልጠየቅም፡፡

ሃትሪክ፡- እርግጠኛ የሆነኮ መረጃ አለኝ…

ምንተስኖት፡- ስህተት ነው ይቅርታ 

አልጠየቀም፡፡

ሃትሪክ፡- ያስያዛችሁትን ክስ 

ቀጠላችሁበት?

ምንተስኖት፡- አዎ ሰው ተወክሎ ክሱን 

እንዲከታተል ተደርጓል፡፡

ሃትሪክ፡- 75 በመቶ የተሸነፍነው በዳኛ 

ነው በሚለው ሃሳብህ ፀንተሃል?

ምንተስኖት፡- ምክንያት አለኝኮ፡፡ ሆን 

ተብሎ እንዲህ በቀይ ከወጣ ቡድኑ የተሟላ 

ስለማይሆን አጨዋወቱ ይወርዳል በሚል 

እሳቤ የተሰራ ይመስለኛል፡፡

ሃትሪክ፡- ፋሲል ኤሌክትሪክን 1ለ0 

በረታበት ጨዋታ የመሃል ዳኛው ለአልሃሰን 

ካሉሺያ የፍፁም ቅጣት ምት ከለከሉ በሚል 

ኤሌክትሪኮች ክስ አስይዘዋል፡፡ ፋሲል በዚህ 

ጨዋታ ተጠቅሟል የሚሉ ወገኖች አሉና 

የዳኝነት ስህተቱ ሁሌም እንዳለ አያሳይም?

ምንተስኖት፡- ማሸነፍ የነበረብንን 

ጨዋታ አሸንፈን ወጥተናል፡፡ በዳኝነቱ በኩል 

ችግር አለ ያሉትን ኤሌክትሪኮችን ብትጠይቅ 

ነው የሚሻለው፡፡ በዚህ ላይ ምንም ማለት 

አልፈልግም፡፡ 

ቡናዎችን ስለዳኝነቱ ብትጠይቅ እንደኛ 

የሚናገሩ ይመስ ልሃል?

ሃትሪክ፡- የነዳዊት እስጢፋኖስ 

አለመኖር አልጎዳችሁም?

ምንተስኖት፡- ቡድኑኮ በአንድ 

ግለሰብ የተወሰነ አይደለም፡፡

ሃትሪክ፡- ማለቴ ሲኒየሮች እነ 

አይናለምን ጨምሮ ሲጎድሉ ጉዳቱ 

አይታይም?

ምንተስኖት፡- አዎ የነአይናለም 

አለመኖር ጎድቶናል፡፡ በዚህም ያለቦታቸው 

እንዲጫወቱ የተደረጉም አሉ ለምሳሌ ሰይድን ያለቦታው መሃል 

ላይ እንዲጫወት አድርገናል የልጆቹ አለመኖር በተ ወሰነ 

መልኩ ውጤቱ ላይ ጎድቶናል፡፡

ሃትሪክ፡- ጫና ውስጥ የመሆን 

ስሜት አልፈጠረብህም?

ምንተስኖት፡- የተሰጠኝን የስራ ድርሻ 

በሚገባ ካልተወጣሁ ነው ጫና ውሰጥ የምገባው፡

፡ በግሌ ይሄ ስሜት አልተሰማኝም ልጆቹም 

ቢሆኑ ያላቸውን አውጥተው ነው የተጠቀሙት 

የክለቡ አመራሮችም ይህን ያዩ ይመስለኛል፡፡ 

እኔን የሚያስጨንቀኝ ሁሌም እንዲህ ያልረባ 

ውሳኔ እየተሰጠ ቡድኔ እንዳይወርድ ነው 

በግሌ በጫና ውስጥ አይደለሁም የስንብት 

ስጋትም የለብኝም፡፡ አንድም ቀን 1 ፐርሰንት 

አስጨንቆኝም አያውቅም፡፡ ለቡድኔ ከሆነ ግን 

እጨነቃለሁ፡፡ ከላይ እንዲሆንም እፈልጋለሁ፡

፡ የአሰልጣኞች ስብስቡ አሪፍ ነው በርግጥ 

አንዳንድ የድለላ ስራዎች አሉ እርሱም ቢሆን 

አያሰጋንም፡፡ በአቅም ደረጃ ሲኒየር የተባሉ 

አሰልጣኞች ውጤትን አይተናል፡፡ ሲኒየሮችን 

እናከብራለን፡፡ ከነርሱም መማር እንፈልጋለን 

ነገር ግን በተሰጠን ሃላፊነት በርትተን እየሰራን 

ስለሆነ ምንም ስጋት የለብንም፡፡

ሃትሪክ፡- የልጆቹ ስሜት የተጎዳ 

ይመስልሃል?

ምንተስኖት፡- ምንም ለውጥ አይኖርም 

ስብስቡ አቅም ያለውና ምርጥ አንድነት 

ያላቸው በመሆኑ ነገም ወደማሸነፍ መመለሳችን 

አይቀርም፡፡ ፋሲል ባልረባ ውሳኔ ተሸንፎ 

የሚፈረካከስ ቡድን አይደለም፡፡

ሃትሪክ፡- ማስተላለፍ የምትፈልገው 

የመጨረሻ መልዕክት አለ?

ምንተስኖት፡- የሚመለከተው አካል ወሳኝ 

ለተባሉ ጨዋታዎች ትኩረት ሰጥቶ ነፃ የሆነ 

ዳኛ ሊመድብ ይገባል፡፡ ጥሩ ጥሩ ኢንተርናሽናል 

ዳኞች አሉን፡፡ በርግጥ ይሄም ኢንተርናሽናል 

አርቢትር ነው ካለው ወቅታዊ ሁኔታ አንፃር ነፃ 

የሆነ ዳኝነት የሚሰጥ አርቢትር እንፈልጋለን፡

፡ በጨዋታ ተበልጠን አምነን ስንሸነፍኮ ደስ 

ይላል እንቀበላለን፡፡ በተዛባ ውሳኔ አገር ላይ 

ተጨዋቾች ላይ መቀለድ ግን ጥሩ አይደለም፡

፡ ሃገርና ህዝብ ወክለን መንቀሳቀሳችን መታወቅ 

አለበት፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

1. ፉአድ ኢብራሂም (ኢትዮጵያ ቡና) : ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ድንቅ የቅጣት ምቶች በነበሩት ጨዋታ ነገሌ ሲያሸንፍ ሀዋሳ በወልዋሎ ነጥብ ጥሏል

7 ጎሎች እና ሁለት ድንቅ የቅጣት ምት ጎሎች በነበሯቸው ሁለት ጨዋታዎች ነገሌ...