መነሻ ገጽ አፍሪካ ፊፋ ጅማ አባጅፋርን ከተጨዋች ዝውውር ማገዱ ተሰማ !
አፍሪካዜናዎችጅማ አባጅፋር

ፊፋ ጅማ አባጅፋርን ከተጨዋች ዝውውር ማገዱ ተሰማ !

አጋራ
አጋራ

 

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተሳታፊው ክለብ ጅማ አባ አፋር የቀድሞውን ጋናዊ ግብ ጠባቂው ዳንኤል አጃይ ደሞዝ መክፈል ባለመቻሉ ምክንያት ለቀጣዮቹ ሶስት የዝውውር መስኮት ከማንኛውም የተጫዋቾች ዝውውር ማገዱን አሳውቋል ፡፡

ከወራት በፊት ጅማ አባ ጅፋር ለተጫዋቹ ቀሪ ክፍያ መፈፀማቸውን የሚያሳይ የሰነድ ማስረጃ እንዲያሟሉ የተጠየቀ ቢሆንም ማስረጃውን አለማቅረባቸው በተገኘው መረጃ ለማወቅ ተችሏል ።

የ 2010 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮናዎች የቀድሞውን የጋና ብሔራዊ ቡድን ኮከብ ግብ ጠባቂ ክፍያ መፈፀማቸውን የሚያሳይ ምንም ዓይነት ሰነድ ማቅረብ አልመቻላቸው ተገልጿል ።

ጅማ አባ ጅፋር የዳንኤልን አጃይን ክፍያ ሙሉ ለሙሉ በከፈለ ሰዓት እገዳው እንደሚነሳ የተጫዋቾች ወቅታዊ ሁኔታ ሀላፊ ኤሪካ ሞንቴሞር ፌሬራ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እና ለጅማ አባ ጅፋር ክለብ በላኩት ደብዳቤ አሳውቀዋል ።


ሀትሪክ ስፖርት የጅማ አባ ጅፋር ስራ አስኪያጅን አቶ ሱልጣንን ለማነጋገር ብንሞክርም ከአጭር የስልክ ቆይታ በኋላ ስልካቸውን ስለዘጉበን ለማግኘት አልተቻለም ።

ሀትሪክ ስፖርት ከክለቡ የውስጥ ምንጭ ለማግኘት እንደቻለችው ጅማ አባ ጅፋር ከዳንኤል አጃይ በተጨማሪ የቀድሞው የክለቡ ተጫዋቾች ዲድዬ ሌብሪ እና ማማዱ ሲዲቤ በተመሳሳይ ክፍያ ያልተፈፀመላቸው ተጫዋቾች መሆናቸውን ለማወቅ ችላለች ። ከዚህ በተጨማሪ ከህዳር ወር አንስቶ አንዳንድ የክለቡ ተጫዋቾች እስከ አሁን ደሞዝ እንዳልተከፈላቸው ለማወቅ ተችሏል ።

ሀትሪክ ስፖርት በቀጣይ የክለቡ ፕሬዝዳንት አቶ አጃኢብን ለማናገር ስትችል ስለ ጉዳዩ የሰሙት ነገር እንደሌለ በመረጃው ከላይ እንደተገለፀው በሚያዚያ ወር ደብዳቤ መላካቸውን እና ከዳንኤል አጃይ በተጨማሪ የዲድዬ ሌብሪ እና ማማዱ ሲዲቤን መረጃ ለፊፋ መላካቸውን ገልፀው ጉዳዩ በሂደት ላይ እንዳለ ብቻ እንደሚያውቁ ገልፀውልናል ።

በቀጣይነት ይህ መረጃ በኢሜል ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሚላክ በመሆኑ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ባህሩ ጥላሁን ብንደውልም ስልካቸው ዝግ በመሆኑ ልናገኛቸው አልቻልንም ።

ሀትሪክ ስፖርት በዚህ ጉዳይ ላይ ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የምታገኘውን መረጃ እንደደረስን የምናቀርብ ይሆናል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሽንፈት ሲገጥመው በድንጉዛ ደርቢ የጦና ንቦቹ እና ኤሌክትሪክ ድል ቀንቷቸዋል

በሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ተከታታይ ሽንፈትን በሸገር ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...