መነሻ ገጽ ሲዳማ ቡና ፈቱዲን ጀማል ከደቂቃዎች በፊት ለሲዳማ ቡና ፈረመ
ሲዳማ ቡናዜናዎች

ፈቱዲን ጀማል ከደቂቃዎች በፊት ለሲዳማ ቡና ፈረመ

አጋራ
አጋራ

በያዝነው የውድድር ዘመን በኢትዮጵያ ቡና ጎልተው ከታዩ ተጫዋቾች አንዱ የሆነው ፈቱዲን ጀማል ከክለቡ ጋር መለያየቱ ዕውን ሆናል

ፈቱዲን ጀማል ከደቂቃዎች በፊት ለቀድሞ ክለቡ ሲዳማ ቡና በመፈረም ከኢትዮጵያ ቡና ጋር በይፋ መለያየቱን አረጋግጧል።
ኢትዮጵያ ቡናና ፈቱዲን ጀማል ከአንድ ወር ቀሪ ደሞዝና ከጥቅማ ጥቅም ጋር በተያያዘ ሲያደርጉት የነበረው ድርድር ፍሬ ሊያፈራ ባለመቻሉ በመጨረሻም ለመለያየትና የተጫዋቹ ማረፊያ ሲዳማ ቡና ሊሆን ችሏል።

የኢትዮጵያ ቡና አሠልጣኝ ካሳዬ አራጌ ወደ ኢትዮጵያ ከመጣ በሃላ ተጫዋቹ ክለቡን እንዳይለቅ በተንቀሳቃሽ ስልኩ ላይ ደውሎ ቢያናግረውም ሊስማሙ ባለመቻላቸው ከቡና ጋር የነበረው ቆይታ በአንድ ዓመት ተጠናቋል።
ፈቱዲን ለሲዳማ ቡና ለሁለት ዓመት የፈረመ ሲሆን የተሻለ ደሞዝና ከፍተኛ ጥቅም እንደቀረበለት ነው የክለቡ ምንጮች በተለይ ለሀትሪክ የገለፁት።
ፈቱዲን ጀማል ከኢት.ቡና ሲለቅ አራተኛው ተጫዋች ሲሆን ከእሱ በፊት አማኑኤል ዮሐንስና አህመድ ሽሪላ ወደ ባህር ዳር፣ግብ ጠባቂው በረከት ወደ መቖለ 70 አንደርታ መዛወራቸው ይታወሳል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...