መነሻ ገጽ ቅዱስ ጊዮርጊስ ፈረሰኞቹ ከ አፄዎቹ የሚያደርጉት ጨዋታ በተመልካች ታጅቦ ይካሄዳል
ቅዱስ ጊዮርጊስየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ፈረሰኞቹ ከ አፄዎቹ የሚያደርጉት ጨዋታ በተመልካች ታጅቦ ይካሄዳል

አጋራ
አጋራ

ነገ በ17ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ኘሪሚዬር ሊግ መርሃ ግብር ፈረሰኞቹ ከ አፄዎቹ የሚያደርጉት ጨዋታ ያለ ተመልካች በዝግ ስታዲዬም ይካሄዳል በሚል ደጋፊዎች ስጋት ቢገባቸውም ጨዋታው በደጋፊዎች ታጅቦ የሚካሄድ ይሆናል፡፡

በ14ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ኘሪሚዬር ሊግ የካቲት 8 ቀን 2010 ዓ/ም በአዲስአበባ ስታዲዬም ቅዱስ ጊዮርጊስ ከአዳማ ከነማ ጋር ባደረጉት ጨዋታ ደጋፊዎች ያልተገባ ስፖርታዊ ጨዋነት አሳይተዋል በሚል የእግር ኳስ የፌደሬሽኑ ዲሲፕሊን ኮሚቴ በቅዱስጊዬርጊስ ስፖርት ክለብ ላይ 180,000 (አንድ መቶ ሰማንያ ሺህ ብር) ቅጣት እና 1 ጨዋታ በዝግ ስታዲዬም እንዲያደርግ ቅጣት መተላለፉ ይታወሳል፡፡

በመሆኑም የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር ይህንን ተከትሎ ለፌደሬሽኑ ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ ይግባኝ በማቅረቡ ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴው ይግባኙን ተቀብሎ የቅጣት ውሳኔው ላይ ማሻሻያ በማድረግ ቅጣቱ ወደ 140,000 (አንድ መቶ አርባ ሺህ ብር) ዝቅ እንዲል እና 1 ጨዋታ በዝግ ስታዲዬም እንዲጫዎቱ የተወሰነው ቅጣትም በይግባኝ ሰሚ ኮሚቴው ውድቅ ሁኗል፡፡

በዚህ መሰረት ቅዱስ ጊዮርጊስ በ17ኛ ሳምንት መርኃ ግብር በነገው ዕለት ከፋሲል ከነማ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ በተመልካች ታጅቦ የሚካሄድ ይሆናል፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና የሊጉን መሪነት ሲያጠናክር ኤሌክትሪክ እና አፄዎቹም አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ሲዳማ ቡና ፣ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ እና ፋሲል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...