መነሻ ገጽ ዜናዎች ድሬዳው ከተማ የአራት ተጨዋቾችን ዝውውር አጠናቋል
ዜናዎችድሬዳዋ ከተማ

ድሬዳው ከተማ የአራት ተጨዋቾችን ዝውውር አጠናቋል

አጋራ
አጋራ

 

በክረምቱ የተጨዋቾች ዝውውር ላይ በርካታ ተጨዋቾቹን ያጣው ድሬዳው አራት ተጨዋቾችን ማስፈረም ችሏል።

ሳሙኤል ዮውሃንስን ለወልዋሎ አሳልፈው የሰጡት ድሬዎች ዘካርያስ ቱጂን ከኢትዮ ኤሌክትሪክ አስፈርመዋል።የፈረሰኞቹ አካዳሚ ውጤት የሆነው ዘካርያስ ቱጂ ሳሙኣል ዬውሃንስ ትቶት የሄደውን ክፍተት ይሸፍናል ተብሎ ይጠበቃል።

አማኑኤል ተሾሙ ሌላኛው ድሬዳዋን የተቀላቀለ ተጨዋች ነው።ባሳለፍነው የውድድር ዓመት ከመከላከያ ጋር ያሳለፈው አማኑኤል ተሾመ ሚኪያስ ትቶት የሄደውን ቦታ ሚሸፍን ይሄናል።

ሥስተኛው የድሬዳዋ ፈራሚ ዋለልኝ ገብሬ ከጅማ ኣባቡና ሆኗል።በግማሽ ዓመት የዝውውር መስኮት ወልዋሎን በመልቀቅ ጅማ አባጅፋርን የተቀላቀለው ዋለልኝ ገብሬ ከ6 ወራት ቆይታ በኃላ ጅፋሮችን በመልቀቅ ድሬዳዋ ከተማን መቀላቀል ችሏል።

አራተኛው ፈራሚ ተከላካዩ ዘሪሁን አንሼቦ ከደቡብ ፖሊስ ሆናል።በዘንድሮው የውድድር ዓመት ከደቡብ ፖሊስ ጋር ወደ ከፍተኛ ሊጉ የወረደው ዘሪሁን አንሼቦ በአንድ ዓመት ውል የቀድሞ ክለቡን ድሬዳዋ ከተማን ተቀላቅሏል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...