መነሻ ገጽ መቐለ 70 እንደርታ ድሬዳዋ ከተማ ያሬድ ሃሰንን አስፈረመ
መቐለ 70 እንደርታዜናዎችድሬዳዋ ከተማ

ድሬዳዋ ከተማ ያሬድ ሃሰንን አስፈረመ

አጋራ
አጋራ

 

ከግማሽ በላይ ቋሚ ተሰላፊዎቹን ያጣው ድሬዳዋ ከተማ የወቅቱ ስድስተኛ ፈራሚያቸውን ያሬድ ሃሰንን አድርገዋል።

ከመቐለ 70 አንደርታ ጋር የሊጉን ዋንጫ ማንሳት የቻለው ያሬድ ሃሰን ባሳለፍነው ውድድር ዓመት በግራ ተከላካይ መስመር ላይ ከአንተነህ ገብረክርስቶስ እና ሄኖክ ኢሳያስ ጋር እየተፈራረቁ መጫወት ችሏል።

ቀደም ብለው ፍሬዘር ካሳን ያስፈረሙት ድሬዎች ያሬድ ሃሰንን ማስመጣታቸው በግራ መስመር ተከላካይ ያላቸውን አማራጭ ሊያሰፋላቸው እንደሚችል ይገመታል።ዋለልኝ ገብረ፣ ፍሬዘር ካሳ፣ዘሪሁን አንሼቦ፣አማኑኤል ተሾመ፣ዘካርያስ ቱጂ በያዝነው የተጨዋቾች ዝውውር መስኮት ድሬዳዋን የተቀላቀሉ ተጨዋቾች ናቸው።

በሳምሶን አባይ ሚመሩት ድሬዎች የቅድመ ውድድር ዝግጅታቸውን መስከረም 10 መቐለ ላይ ይጀምራሉ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...