በኢትዮጵያ ፕሪሚየር 8ኛ ሳምንት በአዲስ አበባ ስታዲየም ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ ድሬዳዋ ከተማ ያደረጉት እና በቅዱስ ጊዮርጊስ 3-2 አሸናፊነት በተጠናቀቀው ጨዋታ ላይ ከጨዋታው ፍጻሜ በኋላ አላስፈላጊ ግርግሮች መፈጠራቸው ይታወሳል። ይህንንም ተከትሎ ድሬዳዋ ከተማ በትናንትናው እለት ለኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን የቅሬታ ደብዳቤ ልኳል። በደብዳቤውም ላይ “ክለባችን የቅዱስ ጊዮርጊስን አስተባባሪዎች መለያ የለበሱ እስከ መልበሻ ቤት ድረስ በመግባት ድብደባ፣ ስድብና የማንገላታት በደል ፈጽመውብናል።” ሲሉ ውሬታቸውን አሰምተዋል። ክለቡ በተጨማሪም “በእለቱ ፀጥታ ሲያስከብሩ የነበሩ አካላት የተፈጠረውን ሁኔታ ከማረጋጋት ይልቅ የቡድናችንን አጠቃላይ የለዕኡካን ቡድን አባላት ከነግርግሩ እዛው ለተቃራኒ ቡድን ደጋፊዎች ጠለውን የሄዱበት ሁኔታ ፍጹም ተቀባይነት የሌለው ነው።” በማለት ገልጿል።
ሙሉ የደብዳቤው ቃል የሚከተለው ነው።

አስተያየት ይስጡ