ትላንትና የሃይማኖት ወርቁን ዝውውር ያጠናቀቁት ደቡብ ፖሊሶች አሁንም ያለፋትን ሁለት አመታት ከመከላከያ ጋር ያሳለፈውን ተመስገን ገብረፃዲቅን ለማስፈረም ከስምምነት ደርሰዋል።
በ2002 ከሀዋሳ ከተማ ወጣት ቡድን ወደ ዋናው ቡድን በማደግ ለተከታታይ 3 ዓመታትን እናት ክለቡን ያገለገለው የአጥቂ መስመር ተጨዋቹ ተመስገን የደቡብ ፖሊስ የወቅቱ 16ተኛ ፈራሚ መሆን ችሏል።
ከሀዋሳ ከተማ በተጨማሪ ለሲዳማ ቡና፣አዳማ ከተማ ና ሀድያ ሆሳእና መጫወት የቻለው ተመስገን ገብረፃዲቅ በቀጣይ አመት በየትኛው የኢትዮጵያ ሊግ አንደሚወዳደር ያላወቀውን ደቡብ ፖሊስን በመቀላቀል የቅድመ ውድድር ዝግጅቱን ሚጀምር ይሆናል።
አስተያየት ይስጡ