መነሻ ገጽ አፍሪካ ደቡብ ሱዳን የወዳጅነት ጨዋታ ልታካሂድ ነው
አፍሪካዜናዎች

ደቡብ ሱዳን የወዳጅነት ጨዋታ ልታካሂድ ነው

አጋራ
አጋራ

 

ወደ እግር ኳሱ በቅርብ ዓመታት ብቅ በማለት አመርቂ ስራዎችን በመስራት ከዓመት ዓመት ተፎካካሪነታቸውን እያሳዩ የሚገኙት ጎረቤት ሀገር ደቡብ ሱዳን በአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያው ከዩጋንዳ ጋር ላለባቸው ጨዋታ መስከረም 30 የወዳጅነት ጨዋታ እንደሚያካሂዱ አሳውቀዋል ።

ደቡብ ሱዳኖች የወዳጅነት ጨዋታቸውን ከ 2017 የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊዋ ካሜሩን ጋር በያውንዴ ጨዋታቸውን እንደሚያደርጉ ይፋ ተደርጓል ።

የደቡብ ሱዳን እግር ኳስ ፌዴሬሽን እንዳስታወቀው ከካሜሩን የወዳጅነት ጨዋታ የቀረበላቸውን ጥያቄ መቀባላቸውን ሲያሳውቁ ከጨዋታው ስምንት ቀናት አስቀድመው በያውንዴ እንደሚከትሙ አሳውቀዋል ።

የብሔራዊ ቡድኑ ዋና አሰልጣኝ ቤሶንግ እንዳስታወቁት በቆይታቸው ከካሜሮን ሊግ ሀያላን ክለቦች እንደ ኮተን ስፖርት እንዲሁም የሊጉ ሻምፒዮን ባሜንዳም ጋር ጨዋታቸውን እንደሚያደርጉ አሳውቀዋል ።

ከዚህ ቀደም ናይጄርያ ፣ ቱኒዚያ ፣ ኮትዲቯር፣ ኬፕ ቨርዴ እንዲሁም ሱዳን የወዳጅነት ጨዋታ እንደሚያካሂዱ ካሳወቁ ሀገራት መካከል ጥቂቶቹ ናቸው ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...