ዮሐንስ ሳህሌ በዛሬው እለት መከላከያን በይፋ ተረክቧል
በፕርሚየር ሊጉ ብሎም በብሔራዊ ቡድን በማሰልጠን ስኬታማ የሚባል ዓመታትን እና ቡድን በመገንባት የሚታወቁት አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ በዛሬው እለት ለመከላከያ መፈረማቸውን ለማወቅ ተችሏል ::
ሀትሪክ ባገኘችው ምንጭ አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ ከዚህ ቀደም የትኛውንም አይነት ስምምነት ከመከላከያ ጋር አለመድረሳቸውን ለማረጋገጥ ሲቻል አሰልጣኙ በቀጣይ አንድ ዓመት በብሔራዊ ሊግ ብርቱ ፉክክር እንደሚጠብቃቸው ይጠበቃል ።
አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ጋር ከተለያዩ በኋላ ያለፉትን ወራት ያለ ክለብ ይገኙ ነበር ።