በቅርብ ጊዜያት ውስጥ በተደጋጋሚ ጊዜያት
ስማቸው ሲጠራ ከከረሙት ኮሚቴዎች አንዱ ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ ነው። ዲሲፕሊን ኮሚቴ ወልዲያ ላይ ከጣለው ቅጣት ጋር በተያያዘ የአንድ አመት የሜዳ ዕገዳን ወደ 3 ጨዋታ በመቀነስ የውዝግቡ መነሻ ሆኗል በሚል የስራ አስፈጻሚው በአቶ ገደቡ መርዕድ የሚመራውን ይህንን ኮሚቴ እንዲበተን መወሰኑ ታውቋል። አመራሮቹ በአስቸኳይ በአዳዲስ አባላት ኮሚቴውን የማጠናከር ስራ ይሰራልም ተብሏል።
በሌላ በኩል ከዚህ ምሽት ጀምሮ ማንኛውም ዳኛና ኮሚሽነር ስላጫወተው ጨዋታ ለሚዲያ መግለጫ እንዳይሰጥ ተከልክሏል።በዚህ መሰሉ ድርጊቱ የተገኘ
ዳኛና ኮሚሽነር ላይም ርምጃ እወስዳለሁ ብሏል
የአርቢትር ኮሚቴው።
አንዳንድ አርቢትሮችምአላስፈላጊና ሃላፊነት የጎደለውን ጸብጫሪ አስተያየታቸውን ማቆም አለባቸው ሲል አርቢትር ኮሚቴው አስጠንቅቋል።
ዳኞችና ኮሚሽነሮች የፊታችን እሁድ ሊጉ ስለሚቀጥል እንዲዘጋጁ ለዚህ ደግሞ ከማህበሩ አመራሮች ጋር ጠንካራ ውይይት እንደሚደረግና ረቡዕ
ለጥያቄው ምላሽ ለመስጠት ስራ አስፈጻሚው እንደሚጥር ከፌዴሬሽኑ የተገኘው መረጃ ያስረዳል።
አስተያየት ይስጡ