ሰርዳን ዝቪጅኖቭ ለዛምብያ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝነት ቢወዳደሩም ሳይሳካላቸው ቀርቷል።
በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤት የተጠበቀውን ያክል ውጤት እያመጡ የማይገኙት አሰልጣኝ ሰርዳን ዝቪጅኖቭ ከሳምንታት በፊት የዛምቢያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ባወጣው የቅጥር ማስታወቂያ ላይ ማስረጃዎቻቸውን ከላኩ አሰልጣኞች መካከል አንደኛው መሆናቸው የዛምቢያ ሚድያዎች በይፋ አስታውቀዋል:: አሰልጣኝ ሰርዳን ዝቪጅኖቭ ምንም እንኳ ማስረጃዎቻቸውን ቢልኩም የመጨረሻ ሶስት እጩዎች ውስጥ ግን መካተት አለመቻሉ ነው የተዘገበው። አሰልጣኙ ለወደፊቱ ከፈረሰኞቹ ጋር ያለው ቋይታስ ምን ይመስላል የሚለው ነገር ተጠባቂ ጉዳይ ያደርገዋል።
አስተያየት ይስጡ