መነሻ ገጽ ዜናዎች የ2012 የተጨዋቾች ዝውውር በኢንተርሚደሪ /ሶስተኛ ወገን/ ብቻ የሚስተናገድ መሆኑ ተገለፀ
ዜናዎችየኢትዮጵያ አንደኛ ሊግየኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዝውውር ዜናዎች

የ2012 የተጨዋቾች ዝውውር በኢንተርሚደሪ /ሶስተኛ ወገን/ ብቻ የሚስተናገድ መሆኑ ተገለፀ

አጋራ
አጋራ

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዓለም አቀፋ እግር ኳስ ፌዴሬሽን /ፊፋ/ የአገር ውስጥና የውጭ አገር ተጨዋቾች ዝውውርን አስመልክቶ ባወጣው መመሪያ መሠረት በቀጣይ በ2012 ዓ.ም ፌዴሬሽኑ በመሚመራቸው ውድድሩሮች ላይ ተሳታፊ የሆኑ ተጨዋቾች በኢንተርሚደሪ /በሶስተኛ ወገን / ብቻ ምዝገባ እንደሚካሄድ አስታወቀ፡፡

ቀደም ሲል ይህንኑ ሥራ ለመስራት የሚያስችለውን የኢንተርሚደሪ /የሶስተኛ ወገን/ ፈቃድ ለሚፈልጉ በሙሉ
በፌዴሬሽኑ መስፈርት መሠረት የፈቃድ መውሰጃ ፈተና በመስጠት 75 የሚሆኑት ተመዝጋቢዎች የመመዘኛ ፈተናውን ማለፋቸውን የአረጋገጡ በመሆናቸው ፈቃዱን ለመውሰድ የፈቃድ ክፍያ እና የኢንሹራንስ ክፍያ በመፈፀም ቅድመ ዝግጅታቸውን እያከናወኑ ይገኛሉ ፡፡

ከሐምሌ 25 /2011 እስከ ጥቅምት 12 /2012 እና ከጥር 1 እስከ ጥር 30 ቀን 2012 ዓ.ም በአንደኛ እና በሁለተኛ ዙር የሚከናወኑት የ2012 ዓ.ም የተጫዋቾች ምዝገባን አስመልክቶ ለኘሪሚየር ሊግ ክለቦች፣ ለከፍተኛ እና ለአንደኛ ሊግ ክለቦች ዛሬ ሐምሌ 18/ቀን 2011 ዓ.ም በተፃፈ ደብዳቤ ከፌዴሬሽኑ ሕጋዊ የሦስተኛ ወገን ፈቃድ በተሰጣቸው ህጋዊ አካላት ብቻ ማስመዝገብ እንደሚገባቸው እና በፌዴሬሽኑ ህጋዊ የሆኑት አካላትም ስም ዝርዝር በደብዳቤ እንደሚላክላቸው የተገለፀ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የአስተዳደር ጉዳዮች ምክትል ፀሐፊ የሆኑት አቶ ሚሊዮን መኮንን ገልፀዋል፡፡
አክለውም “ማንኛውም የአገር ውስጥ እና የውጭ አገር ተጫዋች በተገለፁት የምዝገባ ጊዜያት ለመመዝገብ በሚቀርብበት ወቅት ከፌዴሬሽኑ የሶስተኛ ወገን ፈቃድ ባላቸው እና ሕጋዊ በሆኑት አካላት ብቻ መመዝገብ እንደሚገባቸው” አሳስበዋል፡፡ በመጨረሻም “ይህ አይነቱ አሰራር ለአገራችን እግር ኳስ የራሱ የሆነ በጎ ገጽታ ያለው ሲሆን ለክለቦቻችን በወቅቱ የሚፈጠሩትን የተለያዩ የምዝገባ ስህተቶች በአፋጣኝ ለመፍታት፣ ለፌዴሬሽኑ የገቢ ምንጭ እንዲያገኝ የማስቻል እና ለተጨዋቾች በተደጋጋሚ የሚከሰትን ክስ እና እንግልት ለመቀነስ እንዲሁም የሦስተኛ ወገን ፈቃድ ላላቸው የሥራ እድል መፍጠርን የሚያስችል ነው፡፡ በተጨማሪም የዓለም አቀፋ የእግር ኳስን አሠራር ሂደት የሚከተለውን ዘመናዊ ሥርዓት በአገራችን መተግበሩ በፊፋ እና በካፍ መልካም ገጽታ ለማግኘት የራሱ አስተዋጽኦ እንዲኖረው ያደርጋል በማለት” አስረድተዋል ፡፡

Via- theeff official page

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...