መነሻ ገጽ መከላከያ የ2010 የኢትዮጵያ ዋንጫ ፍፃሜውን ዛሬ ያገኛል።
መከላከያቅዱስ ጊዮርጊስኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ዋንጫዜናዎች

የ2010 የኢትዮጵያ ዋንጫ ፍፃሜውን ዛሬ ያገኛል።

አጋራ
አጋራ

በ2010 ህዳር ላይ የተጀመረው እና በዛው አመት መጠናቀቅ እያለበት በተለያዩ ምክንያቶች እየተጎተተ እና እየተንከባለለ ወደ 2011 የተዛወረው የኢትዮጵያ ዋንጫ ዛሬ ፍፃሜውን የሚያገኝ ይሆናል።

በሀዋሳ አርቲፊሻል ስታዲየም ሲደረግ የቆየው ይህ ውድድር ዛሬ 9:00 ሲል በሀዋሳ ኢንተርናሽናል ስታዲየም መከላከያ ከቅ/ጊዮርጊስ በሚያደርጉት የፍፃሜ ጨዋታ መዝጊያውን የሚያደርግ ይሆናል። በተጠናቀቀው የ2010 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሁለቱ ቡድኖች ተገናኝተው በአንደኛው ዙር 0-0 እንዲሁም በሁለተኛው ዙር ደግሞ 1-1 በሆነ አቻ ውጤት አጠናቀው አመቱን ሳይሸናነፉ ተለያይተዋል። መከላከያ ለተከታታይ 4ኛ ጊዜ የኢትዮጵያ ዋንጫ ፍፃሜ ላይ የሚሳተፍ ሲሆን ቅ/ጊዮርጊስ ደግሞ ከ2006 ዓ.ም በኋላ ከአፍሪካ መድረክ ላለመራቅ ከፍተኛ ፉክክር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

መከላከያ በግማሽ ፍፃሜው ኢትዮጵያ ቡናን በምንይሉ ወንድሙ ብቸኛ ጎል 1-0 በማሸነፍ እንዲሁም ቅ/ጊዮርጊስ ደግሞ ጅማ አባጅፋር በግማሽ ፍፃሜው አልሳተፍም በማለቱ በፎርፌ በማሸነፍ ለፍፃሜ ሊበቁ ችለዋል። ሁለቱ ቡድኖች ከ2006 ጀምሮ 3 ጊዜ ለፍጻሜ የተገናኙ ሲሆን 2006 ላይ በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ 0-0 ተለያይተው መከላከያ በመለያ ምት ሲያሸንፍ በ2008 በመደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ 0-0 ተለያይተው ቅ/ጊዮርጊስ በመለያ ምት አሸናፊ መሆን ችለዋል። ለሶስተኛ ጊዜ በሚገናኙበት የ2010 የኢትዮጵያ ዋንጫ ማን አሸናፊ ይሆናል የሚለው በኢትዮጵያ እግርኳስ አፍቃሪያን ዘንድ ጨዋታውን ተጠባቂ አድርጎታል። ሁለቱ ቡድኖች ከ2008 ጀምሮ በፕሪሚየር ሊጉ 6ጊዜ የተገናኙ ሲሆን 1 ጊዜ መከላከያ 1 ጊዜ ቅ/ጊዮርጊስ ሲያሸንፍ ቀሪዎቹን 4ጨዋታዎች በአቻ ውጤት ማጠናቀቅ ችለዋል።

የሁለቱ ቡድኖች አሸናፊ የዋንጫ ባለቤት ከመሆኑ ባሻገር ከ2010 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አሸናፊው ጅማ አባጅፋር ቀጥሎ በአፍሪካ ውድድር (በአፍሪካ ኮንፌደሬሽን ዋንጫ) ኢትዮጵያን የሚወክል ይሆናል። የሁለቱን ቡድኖች ጨዋታ ኢንተርናሽናል ዳኛ በላይ ታደሰ በዋና ዳኝነት ክንፈ ይልማ እና አበራ አብርደው በረዳት ዳኝነት እንዲሁም ሄኖክ አክሊሉ በአራተኛ ዳኝነት የሚመሩት ይሆናል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጧል የተባለው ዳኛ ተባረረ

በዮሴፍ ከፈለኝ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ አርቢትሮችን ወደመጡበት መመለሱን አሁንም ቀጥሏል። ከቀናት...