የ2010 ፕሪሚየር ሊግ በጅማ አባጅፋር አሸናፊነት ተጠናቆ ክለቦች ከዕረፍት መልስ ወደዝግጅት ገብተዋል በዝውውርም ራሳቸውን እያጠናከሩ ነው።የፌዴሬሽኑ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ባደረገው
ስብሰባ የ2011 ፕሪሚየር ጥቅምት17/2011 እንዲጀመር መወሰኑ ታውቋል። ካለፉት አመታት ተሞክሮ ወደ ዝግጅት ያልገቡ ክለቦች በተወሰነው ቀን ላይ ጥያቄ ማንሳታቸው እንደማይቀር ይጠበቃል።
ካፍ ጥቅምት 5/2011 ድረስ የጥሎማለፍ አሸናፊውን ክለብ አሳውቁ በማለቱ ፌዴሬሽኑ ወደ 2011 የተዛወረው የጥሎማለፍ /የኢትዮጲያ ዋንጫ/
ቀሪ 4 ጨዋታዎችም መስከረም 12 ተጀምረው መስከረም 20 እንዲጠናቀቅ መወሰኑ ተሰምቷል።
ውድድሩ ቶሎ መጠናቀቁ መስከረም 30 ከኬንያ ጋር
ለሚጫወቱት ዋሊያዎቹ የተወሰነ የማገገማያ ጊዜ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።
አስተያየት ይስጡ