መነሻ ገጽ ዜናዎች የፋሲል ከተማ የሊግ ጨዋታዎች በዋልታ ቴሌቪዥን የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ሊያገኝ ነው
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግፋሲል ከተማ

የፋሲል ከተማ የሊግ ጨዋታዎች በዋልታ ቴሌቪዥን የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ሊያገኝ ነው

አጋራ
አጋራ

ፋሲል ከተማ በኢትዮጵያ ኘሪሚዬር ሊግ የሚያደርጋቸው የሁለተኛው ዙር ሁሉም ጨዋታዎች በዋልታ ቴሌቪዥን የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ከየስታዲየሞቹ እንደሚያገኙ የተነገረ ሲሆን የክለቡ ቦርድ ከኤቢ ማስታወቂያና ኤቨንት አዘጋጅ ጋር ከስምምነት ደርሰዋል፡፡

ኤቢ ማስታወቂያና ኤቨንት አዘጋጅ ድርጅት ከዋልታ ቴሌቪዥን ጋር በመተባበር ክለቡ ከሜዳው ውጭና በሜዳው በአፄ ፋሲለደስ ስታዳዬም የሚያደርጋቸው የሁለተኛው ዙር ሁሉም ጨዋታዎች በቀጥታ ስርጭት ሽፋን ለተመልካች እንደሚደርሱ የተነገረ ሲሆን ሞደርን ወርልድ የተባለ ድርጅት በአማካሪነት አብሮ እንደሚሰራ ተነግሯል፡፡

ፋሲል ከተማ ከሜዳው ውጭም ሆነ በሜዳው በሚያደርጋቸው ጨዋታዎች የቴሌቪዥን የምስል መብት ከገቢው 50% የሚያገኝ ሲሆን ተጋጣሚዎቹ 25% የሚያገኙ ይሆናል፡፡

በቀጣይ ጊዜያት የሁሉም ክለቦች ጨዋታ የቴሌቪዥን የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ለመስጠት ኤቢ ማስታወቂያና ኤቨንት አዘጋጅ ድርጅት ከክለቦች ጋር በመነጋገር ላይ መሆናቸውን የተናገሩት የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ አቶ አንተነህ ማሃሪ ከኢትዮጵያ ቡና ወልዲያ ከተማና መከላከያ ክለቦች በተጨማሪ ስማቸው ካልተጠቀሱ 2 ክለቦች ጋር ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ጠቅሰው የስምምነት ውል ፊርማቸውን በቅርቡ በመፈራረም ወደ ስራ እንደሚገቡ ለሀትሪክ ስፖርት ገልፀዋል፡፡

ኤቢ ማስታወቂያና ኤቨንት አዘጋጅ ድርጅት የወልዲያ ከተማና ፋሲል ከተማ የሚዲያ አጋር በመሆን የክለቦቹን ጨዋታዎች ከአማራ መገናኛ ብዙሃን ጋር በመተባበር በክልሉ ኤፌሞችና በመላው አለም በናይል ሳት የሬዲዮ የቀጥታ ስርጭት ከማስተላለፍ ባሻገር በአማራ ቴሌቪዥን “አፄዎቹ”የተሰኘ ኘሮግራም ዘወትር ዕሮብ ምሽት እንደሚያቀርብ ይታወቃል፡፡

ከስፖንሰር ድርጅቶች ጋር የሚያደርጉት ስምምነት ዛሬ የሚያልቅ ከሆነ ፋሲል ከተማ ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ጋር በአዲስ አበባ ስታዲዬም የሚያደርጉት 16ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ጨዋታ በዋልታ ቴሌቪዥን የቀጥታ ስርጭት የሚያገኝ ይሆናል፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ኢትዮጵያ ቡናዜናዎችየዝውውር ዜናዎች

ኢትዮጵያ ቡና ግብ ጠባቂ አስፈረመ

መሳይ አያኖ አዲሱ የኢትዮጵያ ቡና የግብ ዘብ ሆኗል። በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የሚሳተፈው...

ሲዳማ ቡናዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የሲዳማ ቡና ቡድን መሪ ታገደ

በዮሴፍ ከፈለኝ የፕሪምየር ሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና የቡድን መሪው የቀድሞው ዳኛ ዕግድ...

ዜናዎችየዲሲፕሊን ውሳኔዎች

27ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አብዱላጢፍ ባምባ (መቐለ 70 እንደርታ) : ክለቡ ከ ወልዋሎ አዲግራት...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና የሊጉን መሪነት ሲያጠናክር ኤሌክትሪክ እና አፄዎቹም አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ሲዳማ ቡና ፣ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ እና ፋሲል...