መነሻ ገጽ ቅድመ ዳሰሳ የጨዋታ ቅድመ ዳሰሳ/ አዳማ ከተማ ከ አርባምንጭ ከተማ 
ቅድመ ዳሰሳአርባምንጭ ከተማአዳማ ከተማየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የጨዋታ ቅድመ ዳሰሳ/ አዳማ ከተማ ከ አርባምንጭ ከተማ 

አጋራ
አጋራ

ኣዳማ ላይ የሚካሄደው የኣዳማ እና ኣርባምንጭ ጨዋታ ዳሰሳን በክፍል ሁለት ዝግጅታችን እንመለከታለን።
ኣዳማዎች የዋንጫ ተስፋቸውን ለማለምለም ኣርባምንጮች ከወራጅ ቀጠናው ለመውጣት ሚያደርጉት ጨዋታ ዛሬ ከቀኑ 9፡00 ሰዓት በ ኣዳማው ኣበበ በቂላ ስታድየም ይካሄዳል።ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ ቡና የተሸነፋት ኣዳማ የዛሬውን ጨዋታ በማሸነፍ የዋንጫ ተፎካካሪ መሆናቸውን ማሳየት ይፈልጋሉ።ኣርባምንጭም ከወላይታ ድቻ የጣሉትን 2 ነጥብ ለማካካስ ወደ ሜዳ ይገባሉ ግን ከሜዳቸው ሲወጡ የሚያሳዩት ደካማ ኣቋም ለወራጅ ስጋት ያጋለጣቸው ዋና ምክንያት ነው።
4-2-3-1 የጨዋታ ስልት ሚከተሉት ኣዳማ የዳዋ ሆቴሳ እና የከንኣን ማርክነህ ጥምረት ከሜዳው ሲወጣ ለሚቸገረው የኣርባምንጭ ተከላካይ ፈተና ይሆንባቸዋል።በተለይ ኣጥቂው ዳዋ ሆቴሳ ወደ መስመር እየወጣ ሚየደርጋቸው እንቅስቃሴ ለሌሎች የቡድን ኣጋሮቹ ክፍተትን ይፈጥራል።
ኣርባምንጭም በ 4-1-4-1 ጨዋታ ስልት በግራ መስመር በሚጫወተው እንዳለ ከበደ በሚነሱ ኳሶች የጎል ዕድል ሚፈጥሩት ኣርባምንጭ ኣጥቂ ስፍራ ሚጫወተው ተመስገን ካስትሮም የቡድኑ ሌላ የማጥቃት ኣማራጭ ነው። 
አዳማ ከተማ በዛሬው ጨዋታ ጃኮ ፔንዜ እና በረከት ደስታበቅጣት አይሰለፉም።በአርባምንጭ በኩሉ የጉዳት እና የቅጣት ዜና የለም።

ጨዋታው ኢንተርናሽናል ዳኛ ለሚ ንጉሴ በመሃል ዳኝነት ይመራዋል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሽንፈት ሲገጥመው በድንጉዛ ደርቢ የጦና ንቦቹ እና ኤሌክትሪክ ድል ቀንቷቸዋል

በሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ተከታታይ ሽንፈትን በሸገር ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

የ30ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች መናፍ ዐወል (አዳማ ከተማ): ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ...