ኣዳማ ላይ የሚካሄደው የኣዳማ እና ኣርባምንጭ ጨዋታ ዳሰሳን በክፍል ሁለት ዝግጅታችን እንመለከታለን።
ኣዳማዎች የዋንጫ ተስፋቸውን ለማለምለም ኣርባምንጮች ከወራጅ ቀጠናው ለመውጣት ሚያደርጉት ጨዋታ ዛሬ ከቀኑ 9፡00 ሰዓት በ ኣዳማው ኣበበ በቂላ ስታድየም ይካሄዳል።ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ ቡና የተሸነፋት ኣዳማ የዛሬውን ጨዋታ በማሸነፍ የዋንጫ ተፎካካሪ መሆናቸውን ማሳየት ይፈልጋሉ።ኣርባምንጭም ከወላይታ ድቻ የጣሉትን 2 ነጥብ ለማካካስ ወደ ሜዳ ይገባሉ ግን ከሜዳቸው ሲወጡ የሚያሳዩት ደካማ ኣቋም ለወራጅ ስጋት ያጋለጣቸው ዋና ምክንያት ነው።
4-2-3-1 የጨዋታ ስልት ሚከተሉት ኣዳማ የዳዋ ሆቴሳ እና የከንኣን ማርክነህ ጥምረት ከሜዳው ሲወጣ ለሚቸገረው የኣርባምንጭ ተከላካይ ፈተና ይሆንባቸዋል።በተለይ ኣጥቂው ዳዋ ሆቴሳ ወደ መስመር እየወጣ ሚየደርጋቸው እንቅስቃሴ ለሌሎች የቡድን ኣጋሮቹ ክፍተትን ይፈጥራል።
ኣርባምንጭም በ 4-1-4-1 ጨዋታ ስልት በግራ መስመር በሚጫወተው እንዳለ ከበደ በሚነሱ ኳሶች የጎል ዕድል ሚፈጥሩት ኣርባምንጭ ኣጥቂ ስፍራ ሚጫወተው ተመስገን ካስትሮም የቡድኑ ሌላ የማጥቃት ኣማራጭ ነው።
አዳማ ከተማ በዛሬው ጨዋታ ጃኮ ፔንዜ እና በረከት ደስታበቅጣት አይሰለፉም።በአርባምንጭ በኩሉ የጉዳት እና የቅጣት ዜና የለም።
ጨዋታው ኢንተርናሽናል ዳኛ ለሚ ንጉሴ በመሃል ዳኝነት ይመራዋል።
አስተያየት ይስጡ