የጨዋታ ቅድመ ዕይታ| አዳማ ከተማ ከ ሀድያ ሆሳዕና
ጨዋታ : አዳማ ከተማ ከ ሀድያ ሆሳዕና
የጨዋታ ቀን: እሁድ ጥር 17/5 2012
የጨዋታ ሰአት :9:00
የጨዋታ አርቢተር: ኢንተ አርቢትር ዶ/ር ሃ/የሱስ ባዘዘው
የጨዋታው ቦታ:አዳማ አበበ በቂላ ስቴዲየም
የኢትዮጲያ ፕሪምየር ሊግ 10ኛ ሳምንት ላይ ሲደርስ ቅዳሜ እና እሁድ ደግሞ ጨዋታዎቹ ይከናወናሉ ነገ ቅዳሜ ሶስት እሁድ ቀሪ አምስት ጨዋታዎች የሚካሄዱ ይሆናል፡፡ በነገው እለት በአዳማ አበበ በቂላ ስታየም የሚካሄድውን የአደማ ከተማ እና ሀድያ ሆሳዕና ጨዋታ እንደሚከተለው በቅድመ ዕይታ ዳሰሳችን እንደሚከተለው አሰናድተንላችኋል።
አዳማ ከተማዎች ጥሩ ጅማሮን በሊጉ ቢያሳዩም በክለቡ ውስጣዊ ችግሮች እየታመሱ አስከፊ የሊገ ጉዞ ከሚያደርጉ ክለቦች ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛሉ ፡፡
በሊጉ ለመጨረሻ ጊዜ ማሸነፍ የቻሉት በሁለተኛው ሳምንት ከአዲስ አዳጊው ወልቂጤ ከተማ ጋር ባደረጉት ጨዋታ ሲሆን በተቀሩት አምስተ ጨዋታዎች ላይ የአቻ ወጤት ሲያስመዘግቡ በሁለት ጨዋታዎች ላይ ተሸንፈዋል ፡፡
ሀድያ ሆሳዕናዎች በተቃራኒው ደካማ የሊግ ጅማሮን ቢያደርጉም የኋላ ኋላ ግን በሊጉ ፈታኝ እየሆኑ ክለቦች ተርታ ለመቀመጥ ችለዋል ፡፡
ሀድያ ሆሳዕና በኢትዮጰያ ቡና አስከፊ ሽንፈት ካጋጠማቸው በኋላ ባደረጉት የሊጉ ሶስት መርሀ ግብሮች ላይ በተከታታይ ጨዋታዎች ላይ ሽንፈት አልገጠማቸውም ፡፡
በሊጉ ጠንካራ ፉከክር እያደረጉ ያሉትን ሲዳማ ቡነ ፤ ወልዋሎን ሲያሽንፉ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ነጥብ መጋራት ችለዋል ፡፡
ሁለቱም ቡድኖች በእኩል ነጥብ ላይ ተቀምጠው በጎል ክፍያ ተበላልጠው በሊጉ ግርጌ ላይ ሲገኙ አሸናፊው ቡድን በደረጃ ሰንጠረዡ የሌሎች ቡድኖች ውጤትን ጠብቀው እስከ ስምንተኛ ደረጃ የሚያስቀምጣቸውን ውጤት ሊያስመዘግቡ ይችላሉ ፡፡
አስተያየት ይስጡ