መነሻ ገጽ ዜናዎች “የጥሎ ማለፉ ብቻ ሳይሆን የፕሪምየር ሊጉም አሸናፊ እኛ ነን” ሱራፌል ዳኛቸው (ፋሲል ከነማ)
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግፋሲል ከተማ

“የጥሎ ማለፉ ብቻ ሳይሆን የፕሪምየር ሊጉም አሸናፊ እኛ ነን” ሱራፌል ዳኛቸው (ፋሲል ከነማ)

አጋራ
አጋራ

ሱራፌል፡- የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
ዋንጫን እኛ አላጣነውም አሁንም ራሳችንን
እንደሻምፒዮና ቡድን አድርገን ነው
እየቆጠርን የምንገኘውና የእሁዱን የጥሎ
ማለፍ ዋንጫ ማግኘታችን ሁላችንንም
ደስተኛ አድርጎናል፡፡
ሀትሪክ፡- የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ
አሸናፊ የተባለው ፋሲል ከነማ ሳይሆን
መቐለ 70 እንደርታ ተብሏል፤ አንተ ግን
ሻምፒዮናው እኛ ነን እያልክ ነው፤ ከምን
በመነሳት ነው?
ሱራፌል፡- የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ
የዘንድሮ የውድድር ዘመን ተሳትፎአችን
ላይ ክለባችን ብዙ ጥሮ ብዙ ለፍቶ ብዙ
መስዋዕትነት ከፍሎ ሽረ ላይ ከኳስ በወጣ
እና በታየው አስቀያሚ ነገር ይኸውም
እግር ኳሳዊ ባልሆነ ሁኔታ በዕለቱ
ፖለቲካዊ ነገሮች በተንፀባረቀበት ሁኔታ
ዋንጫውን ከመድረክ ባንቀበልም አሁንም
በድጋሚ መናገር የምፈልገው የውድድሩ
አሸናፊ እንደሆንን የምንቆጥረው ራሣችንን
ነው፡፡
ሀትሪክ፡- ፋሲል ከነማ በአፍሪካ
ኮንፌዴሬሽን ካፕ ላይ ይሳተፋል፤
ስለውድድሩ ተሳትፎ እና ስለሚመዘገበው
ውጤት ምን ትላለህ?
ሱራፌል፡- የአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን
ካፕ ላይ ቡድናችን የሚኖረው ተሳትፎ
ከውድድሩ ባሻገር ለእኛም ተጨዋቾች
የፕሮፌሽናል ተጨዋቾችንን ዕድል
የሚያስገኝልን ስለሆነ ለጨዋታው እየሰጠን
ያለው ትኩረት ከፍ ያለ ነው፤ ለውድድሩም
በአጭር ጊዜ ውስጥ ዝግጅታችንን እንጀ
ምራለን፤ የአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ካፕ ላይ
በሚኖረን ውድድርም ቡድናችን ግጥሚ
ያውን የሚያደርገው ለተሳትፎ ሳይሆን
የፋሲል ከነማ እግር ኳስ ክለብ እሁድ እለት ሐዋሳ ከተማን አሸንፎ የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ዋንጫን ካነሳ
በኋላ የቡድኑ አሰልጣኝ ውበቱ አባተ እና የቡድኑ ተጨዋች
ሱራፌል ዳኛቸው ስለ ድሉ እና ሌሎች ላቀረብንላቸው ጥያቄ
የሚከተለውን ምላሽ ሊሰጡን ችለዋል፡፡
ጥሩ ውጤት ለማምጣት ነው፤ ፋሲል ከነማ
ጠንካራ እና ጥሩ አቅም ያለው ቡድን
ነውና ለመጀመሪያ ጊዜ በሚኖረን ተሳትፎ
እኛነታችንን ማሳየት እንፈልጋለን፤ ይሄ
እንደሚሳካልንም አምናለሁ፡፡
ሀትሪክ፡- ፋሲል ከነማ የጥሎ
ማለፉን ዋንጫ ያነሳበትን ጨዋታ እንዴት
ትመለከተዋለህ?
ሱራፌል፡- የሐዋሳ ከነማ ክለብን በፍፁም
ቅጣት ምት ያሸነፍንበት ጨዋታ ሜዳው
የአንድ ሁለት ቅብብልንም ሆነ ድሪብል
አድርገህ ጥሩ ለመጫወት የማትችልበት
ነበርና በዚህ በኩል በእንቅስቃሴው በኩል
ተቸግረናል፡፡ ያም ሆኖ ግን ሀዋሳዎች ግብ
በማስቆጠር እኛን ቢቀድሙንም ቡድናችን
ጎል እንደሚያስቆጥር ለአሰልጣኛችን ውበቱ
አባተ እየነገርኩት ነበርና ያንን ነው
በማሳካት በመጨረሻም በፍፁም ቅጣት ምት
ለማሸነፍ የቻልነው፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
መቐለ 70 እንደርታዜናዎች

ገረሱ ሸመና መቐለ 70 እንደርታን ተቀላቀለ

በሊጉ ለመቆየት እየዳዱ የሚገኙት መቐለ 70 እንደርታዎች ረዳት አሰልጣኝ ሾመዋል። በኢትዮጵያ እግር...

ወላይታ ድቻዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

“የቀዶ ጥገና ህክምና ይደረግለታል” የወላይታ ድቻ ስራ አስኪያጅ አቶ ምትኩ ሐይሌ

ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም ከባድ ጉዳትን ያስተናገደው ወጣቱ ተጫዋች ቅዱስ ቂርቆስ በምን...

ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...