መነሻ ገጽ ዜናዎች የጀርመኑ ባየርሙኒክ እግር ኳስ ክለብ የተለያዩ ሥልጠናዎችን ለመስጠት ባለሙያዎችን ወደ አዲስ አበባ ሊልክ ነው፡፡
ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

የጀርመኑ ባየርሙኒክ እግር ኳስ ክለብ የተለያዩ ሥልጠናዎችን ለመስጠት ባለሙያዎችን ወደ አዲስ አበባ ሊልክ ነው፡፡

አጋራ
አጋራ

ባየርሙኒክ እግር ኳስ ክለብ ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር ቀደም ሲል የልምድ ልውውጥ፣ ተከታታይ የወጣት አሰልጣኞች ስልጠናት እና ቀጣይነት ያላቸውን ሥራዎች ለመስራት ባደረገው ስምምነት መሠረት የካቲት 8 ቀን 2012 ዓ.ም ባለሙያዎችን ወደ አዲስ አበባ በመላክ የ15 ቀናት ቆይታ በማድረግ የተለያዩ ሥራዎችን የሚሰራ ይሆናል፡፡
የባየርሙኒክ እግር ኳስ ክለብ ቀደም ሲል ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር በመተባበር በርካታ ስልጠናዎች እና የልምምድ ልውውጦችን የአደረገ ሲሆን በቀጣይ ቆይታው የተለያዩ ሥራዎችን ለመስራት ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የቴክኒክና ልማት ዳይሬክቴሬት ጋር ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡
በመጀመሪያው ኘሮግራም ቀደም ሲል በሁለት ዙር ከየክልሉ ለተውጣጡ የጀማሪ ወጣት አሰልጣኞች በተሰጠው ስልጠና ተገቢውን ውጤት ላሟሉ እና ወደ ቀጣይ ዙር ላለፋ 30 ወጣት አሰልጣኞች ለተከታታይ 5 ቀናት ከሰኞ የካቲት 9 እስከ የካቲት 13 ቀን 2012 ዓ.ም የቀጣይ ዙር ስልጠና ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ስታዲየም የሚሰጥ ይሆናል፡፡
በተከታይነትም ለኢትዮጵያ ኘሪሚየር ሊግ የወንዶች ክለቦች እና ለ1ኛ ዲቪዚዮን የሴቶች ኘሪሚየር ሊግ ክለቦች አሠልጣኞች የሙያ ማሻሻያ ሥልጠና ከየካቲት 16 እስከ የካቲት 18 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ ለሦስት ተከታታይ ቀናት የሚሰጥ ሲሆን በየካቲት 19 እና 20 /2012 ዓ.ም ኘሮግራሙ በባየር ወጣቶች ዋንጫ ላይ ተሳታፊ የሚሆኑ ከ15 ዓመት በታች ታዳጊዎችን በመመልመል እና 10 ተጫዋቾችን በመለየት በሚያዚያ መጨረሻ በጀርመን ሙኒክ ከተማ ላይ ለሚካሄደው የባየር የታዳጊዎች ዋንጫ ውድድር ላይ ተሳታፊ የሚሆኑበት እድል የሚፈጠር ሥራዎችን የሚሰራ ይሆናል፡፡

Via – EFF

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

ዋልያዎቹ በአሜሪካ የወዳጅነት ጨዋታን ሊያደርጉ ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ አሜሪካ ሊያመራ ነው ነገር ግን የወቅቱ የብሔራዊ ቡድኑ...