መነሻ ገጽ ዜናዎች የድሬዳዋ ስታድየም እድሳት በመገባደድ ላይ ይገኛል
ዜናዎችድሬዳዋ ከተማ

የድሬዳዋ ስታድየም እድሳት በመገባደድ ላይ ይገኛል

አጋራ
አጋራ

_______________________________________

ባሳለፍነው ዓመት እድሳቱን የጀመረው ኣንጋፋው ድሬዳዋ ስታድየም ጨዋታ ለማስተናገድ የሚያስችሉት ሁኔታዎች ከሞላ ጎደል ማጠናቀቅ ችሏል።የመቀመጫ ወንበር፣የመጫወቻ ሜዳ እንዲሁም የመሮጫ መም ላይ ትኩረት ያደረግው የድሬዳዋ ስታድየም እድሳት በቅርቡ ተጠናቆ ለውድድር ዝግጁ እንደሚሆን ለማወቅ ተችሏል።

በ1969 በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት በተካሄደው 3ኛው አፍሪካ ዋንጫ ስድስት ጨዋታዎችን ማስተናገድ የቻለው እንዲሁም በ2007 ኢንተርናሽናል ጨዋታዎችን የማስተናገድ ፍቃድን ከካፍ ያገኛው እድሜ ጠገቡ ድሬዳዋ ስታድየም ሙሉ በሙሉ እድሳቱን ሲጨርስ ኢንተርናሽናል ጨዋታዎችን ሚያስተናግድ ይሆናል።

የመጫዋቻንና መቀመጫውን በአዲስ መልክ እየቀየረ ያለው አንጋፋው #የድሬዳዋ_ስታዲየም የመጫወቻው ሜዳ ሣር ለ2ኛ ጊዜ ሰሞኑን ይታጨዳል።
የመጀመሪያ ዙር ከታጨደ በኋላ በተሻለ ሁኔታ ጥቅጥቅ ብሎ የበቀለው ሣሩ ለጨዋታ ዝግጁ ለመሆን የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ እንደደረሰ ባለሙያዎች ተናግረዋል።
በሜዳው ዙሪያ ያለው የውሃ ማሶገጃ ቦዩ በፍርግርግ ብረት የመድፈኑ ስራ የተጀመረ ሲሆን ከፈጠነ በ2 ሳምንት ጊዜ ውስጥ ሊጠናቀቅ እንደሚችል ተጠቁሟል።
የሜዳው ሥራ ከፈጠነ በታህሳስ ወር አጋማሽ ለጨዋታ ዝግጁ እንደሚሆን ባለሙያዎች ተናግረዋል።፥
ምንጭ -የክለቡ የፋዊ ገፅ

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሽንፈት ሲገጥመው በድንጉዛ ደርቢ የጦና ንቦቹ እና ኤሌክትሪክ ድል ቀንቷቸዋል

በሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ተከታታይ ሽንፈትን በሸገር ሲያስተናግድ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...