መነሻ ገጽ ወልዋሎ “የወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ አሰልጣኝ ዮሃንስ ሳህሌ ቡድኑ ጋር እንደሌሉና የት እንዳሉም እንደማያውቁ የክለቡ ስራ አስኪያጅ ገለጹ”
ወልዋሎዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

“የወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ አሰልጣኝ ዮሃንስ ሳህሌ ቡድኑ ጋር እንደሌሉና የት እንዳሉም እንደማያውቁ የክለቡ ስራ አስኪያጅ ገለጹ”

አጋራ
አጋራ

👉👉የወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ አሰልጣኝ ዮሃንስ ሳህሌ ቡድኑ ጋር እንደሌሉና የት እንዳሉም እንደማያውቁ የክለቡ ስራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡ የክለቡ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ አማረ

“ከአሰልጣኙ ጋር ያለው ጉዳይ አልየለትም የት እንዳሉም አናውቅም ባለፉት ሁለት ቀናት በነበረው ልምምድ ላይም አልነበሩም ቡድኑ በሚገኝበት ሆቴልም ውስጥም የሉም ምክንያቱ ምን እንደሆነ ስላላወቅን እየጠበቅናቸው ነው ቦርዱም በጉዳዩ ላይ ተሰብስቦ ውሳኔ ገና አልሰጠም በቀጣይ የሚሆነውን አብረን የምናየው ይሆናል” በማለት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

የፌዴሬሽኑ የዲሲፕሊን ኮሚቴ በ9ኛው ሳምንት ጨዋታ ወልዋሎ አዲግራት በባህርዳር ከተማ 3 ለ 2 በተረታበት ጨዋታ የአርቢትሩ ለሚ ንጉሴን ውሳኔ በመቃወም ግጥሚያው 13 ደቂቃ እንዲቋረጥ አድርገዋል በሚል የጨዋታና የገንዘብ ቅጣት ያስተላለፈው እንደሌሎቹ አሰልጣኞችና ክለቦች ጠርቶ ሳያናግራቸው መሆኑ ከደንቡ አንጻር ተገቢ አይደለም በሚል ጥያቄ ማስነሳቱ ታውቋል፡፡ አሰልጣኙ ከክለቡ ጋር ያላቸው ግንኙነት ከመቋረጡም በላይ ክለቡና አመራሮቹ አስፈላጊ ድጋፍ አልሰጡኝም በሚል ለከፍተኛ የክለቡ አመራሮች የስራ መልቀቂያ ደብዳቤ ማስገባታቸውም እየተነገረ ይገኛል፡፡

በመጀመሪያዎቹ 10 ጨዋታዎች 8 ግብ ብቻ የተቆጠረበት ወልዋሎ አዲግራት ባለፉት 3 ጨዋታዎች ግን 9 ግብ ማስተናገዱ ተጨዋቾቹ ላይ የደረሰውን የስነልቦና ጉዳትና በራስ መተማመናቸው መውረድን ያሳያል ተብሏል፡፡አሰልጣኙ ቀሪ 2 ጨዋታዎች ላይም ቡድናቸውን የማይመሩ በመሆኑ ምናልባት ሃሳባቸውን ቢቀይሩ እንኳን በቴክኒክ ቦታው ላይ ቡድናቸውን የሚመሩት በ2ኛ ዙር ላይ ይሆናል፡፡ በ14ኛው ሳምንት የሊጉ መርሃግብር ወልዋሎ አዲግራት በቀጣዩ እሁድ አዳማ ላይ ከሜዳ ውጪ አዳማ ከተማን ይገጥማል፡፡

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...